![](https://ethioagri.com/wp-content/uploads/2024/07/452616139_1037804088346234_6853105405740841269_n-848x480.jpg)
የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም የተቋሙ የማኔጅመንት አባላት እና የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ሥራ አስኪያጆች በተገኙበት እየተገመገመ ነው።
ግምገማው በነገው ዕለትም የሚቀጥል ሲሆን፣ ነገ የኮርፖሬሽኑ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ይደረጋል።
###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው! ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም
![](https://ethioagri.com/wp-content/uploads/2024/07/452616139_1037804088346234_6853105405740841269_n-1024x478.jpg)
![](https://ethioagri.com/wp-content/uploads/2024/07/452532481_1037804151679561_8212419314339472398_n-1024x478.jpg)
![](https://ethioagri.com/wp-content/uploads/2024/07/452514062_1037803721679604_6426252061389370037_n-1024x495.jpg)
![](https://ethioagri.com/wp-content/uploads/2024/07/452513282_1037804085012901_5908830253632244197_n-1024x523.jpg)
![](https://ethioagri.com/wp-content/uploads/2024/07/452479633_1037804121679564_3258254177040278455_n-1024x478.jpg)
![](https://ethioagri.com/wp-content/uploads/2024/07/452403751_1037804061679570_2560678635318876658_n-1024x478.jpg)
ግምገማው በነገው ዕለትም የሚቀጥል ሲሆን፣ ነገ የኮርፖሬሽኑ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ይደረጋል።
###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው! ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም
* በሌላ ዜና ለኮርፖሬሽኑ የውስጥ አገልግሎት የሚውሉ የዳቦ መጋገሪያ እና የጉድጓድ ውኃ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ያስገነባውን የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም አስመረቀ። ወይዘሮ አስናቀች ፀጋ ለተባሉ የወረዳ 6 ነዋሪ ከ1 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባውን መኖሪያ ቤት በመመረቅ ቁልፍ የአስረከቡት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የወረዳ 6 አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቶፊቅ ከድር ናቸው። በዚሁ ወቅት ንግግር የአደረጉት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ኮርፖሬሽኑ የሕዝብ ተቋም እንደመሆኑ ለሕዝብ ያለውን አጋርነት ለማረጋገጥ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛል ብለዋል። ኮርፖሬሽኑ ባለፉት ዓመታት ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር እና ከሚያገኘው ትርፍ ላይ በየዓመቱ ለማኅበራዊ ኃላፊነት በጀት በመመደብ በተለያዩ አካባቢዎች ለበርካታ ማኅበረሰቦች የገንዘብ እና የቁሳቁስ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አቶ ክፍሌ አብራርተዋል፡፡ አክለውም ኮርፖሬሽኑ በ2016 በጀት ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን ከማስቀጠል ባሻገር ለተለያዩ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ከ16 ሚሊየን ብር በላይ ማውጣቱን ጠቁመው፣ ከአከናወናቸው ሥራዎች አንዱ የወይዘሮ አስናቀች ፀጋ መኖሪያ ቤት ግንባታ መሆኑን አስታውቀዋል። የወረዳ 6 አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቶፊቅ ከድር በበኩላቸው፣ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በመተባበር በርካታ ሰው ተኮር የሆኑ ሥራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ ጠቁመው፣ ኮርፖሬሽኑ የአስገነባው የአስፋልት መንገድ፣ አጥር እና ሌሎች የግቢ ማስዋብ ሥራዎች የአካባቢውን ገጽታ በተሻለ መልኩ መቀየራቸውን ተናግረዋል፡፡ ኮርፖሬሽኑ አርሶ አደሩን ብቻ ሳይሆን የከተማ ነዋሪዎችንም ጭምር ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ቶፊቅ፣ የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት ሥራ፣ የውኃ እና ጎርፍ ማፋሰሻ ተግባራት ለዚህ ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ በዚህ የተነሳም የአካባቢው ነዋሪ ኮርፖሬሽኑን እንደ እራሱ ንብረት እያየው ይገኛል ብለዋል። በኮርፖሬሽኑ የውስጥ አቅም የተገነባው የወይዘሮ አስናቀች መኖሪያ ቤት በብሎኬት የተሰራ ሲሆን፣ የቀድሞውን እድሜ ጠገብ አሮጌ ቤት አፍርሶ ለመገንባት የሦስት ወራት ጊዜ ወስዷል፡፡ 7መኖሪያ ቤቱ ማብሰያ ቤትን ጨምሮ አራት ክፍሎች ያሉት ሲሆን፣ የቤት ውስጥ ቁሳቁስ ተሟልቶለታል፡፡ በመርሐ ግብሩ ማጠቃለያ ኮርፖሬሽኑ በ2016 በጀት ዓመት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ለአበረከተው የልማት አስተዋጽዖ ከክፍለ ከተማው የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶለታል። በሌላ ዜና ለኮርፖሬሽኑ የውስጥ አገልግሎት የሚውሉ የዳቦ መጋገሪያ እና የጉድጓድ ውኃ ፕሮጀክቶች ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ተመርቀዋል። የውኃ ፕሮጀክቱ በተደጋጋሚ ያጋጥም የነበረን የውኃ እጥረት ያቃለለ ሲሆን፣ ዳቦ ቤቱ ደግሞ ለኮርፖሬሽኑ ሠራተኞች በተመጣጣኝ ዋጋ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። በቀጣይም ለአካባቢው ማኅበረሰብ ዳቦ እና እንቁላል ለማቅረብ ታስቧል።
ግብርናን ከማዘመን ጎን ለጎን ማኅበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት ለሕዝብ ያለንን አጋርነት እናረጋግጣለን!
* “የዛሬው ዕለት ለኮርፖሬሽኑ ታሪካዊ ቀን ነው” የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ
* “የሀገሪቱ የምጣኔ ሀብት እድገት የጀርባ አጥንት ለሆነ ተቋም የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት እንዲተገብር የማማከር እና የመደገፍ ሥራ እያከናወንን በመሆኑ ታላቅ ደስታ እና ኩራት ይሰማናል” የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት የሙከራ ትግበራ ጀመረ፡፡
በኮርፖሬሽኑ የስብሰባ አዳራሽ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በተካሄደ የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት የሙከራ ትግበራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር፣ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም እንደተናገሩት፣ ዕለቱ ኮርፖሬሽኑ የISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን በመተግበር ከዓለም አቀፍ ተቋማት መካከል አንዱ የሚያደርገው ታሪካዊ ቀን ነው ብለዋል፡፡አክለውም ሁሉም የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች የአሠራር ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲሆን በቁርጠኝነት በመስራት አሻራቸውን እንዲያኖሩ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡አያይዘውም የአሠራር ሥርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ላይ አስተዋጽዖ ለአበረከቱ በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በሙከራ ትግበራ ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሰረት በቀለ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ “የሀገሪቱ የምጣኔ ሀብት እድገት የጀርባ አጥንት ለሆነ ተቋም የISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት እንዲተገብር የማማከር እና የመደገፍ ሥራ እያከናወንን በመሆኑ ታላቅ ደስታ እና ኩራት ይሰማናል” በማለት ተናግረዋል፡፡አክለውም ኮርፖሬሽኑ የሰነድ ሥራዎችን እና ሌሎች ቅድመ ዝግጅቶችን በአጭር ጊዜ አከናውኖ ወደ ሙከራ ትግበራ መግባቱ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመው፣ የተቋሙን ሥራ አመራር እና ሠራተኞች እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል፡፡ ISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ለመተግበር ከፍተኛ ቁርጠኝነት እንደሚጠይቅ የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ፣ በዚህ ረገድ የኮርፖሬሽኑ አመራሮች እና ሠራተኞች ያላቸው ቁርጠኝነት የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን መተግበር በትርፋማነት እና አሠራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣል ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ፣ ተቋማቸው ኮርፖሬሽኑ የአሠራር ሥርዓቱን ሙሉ በሙሉ እንዲተገብር በተለየ ሁኔታ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የሙከራ ትግበራ ሥራው እስከ መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን፣ የኮርፖሬሽኑ ሠራተኞች ሥርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጁ እና ቁርጠኛ መሆናቸውን በሰጡት አስተያየት አስታውቀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በዕለቱ መርሐ ግብር የISO ዶክመንት ርክክብ የተደረገ ሲሆን፣ ሰነዶቹን ለአራት የዘርፍ ኃላፊዎች የአስረከቡት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ናቸው፡፡ በሌላ በኩል ከኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት እና ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ተውጣተው የISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት የአተገባበር ሥልጠና የወሰዱ 39 ሠራተኞች ከኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሰረት በቀለ (ዶ/ር) እጅ የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል፡፡
###
የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን በመተግበር ግብርናን የማዘመን ግባችንን እናሳካለን!
ሮቤ፣ ሐምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በባሌ ሮቤ ከተማ 1 ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ ያስገነባው የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ሐምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተመርቆ የቁልፍ ርክክብ ተፈጽሟል።
ኮርፖሬሽኑ መኖሪያ ቤቱን ያስገነባው በሮቤ ከተማ በሃቢፍቱ ቀበሌ ነዋሪ ለሆኑት ወይዘሮ መክዳ አብዱራሂም ነው።
በምረቃ እና በቁልፍ ርክክብ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም በአደረጉት ንግግር፣ ኮርፖሬሽኑ የሕዝብ ተቋም እንደመሆኑ ለሕዝብ ያለውን አጋርነት ለማረጋገጥ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛል ብለዋል።
በዕለቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከሮቤ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን መኖሪያ ቤቱን መርቀው ለወይዘሮ መክዳ አብዱራሂም ቁልፍ አስረክበዋቸዋል። ኮርፖሬሽኑ ባለፉት ዓመታት ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር እና ከሚያገኘው ትርፍ ላይ በየዓመቱ ለማኅበራዊ ኃላፊነት በጀት በመመደብ በተለያዩ አካባቢዎች ለበርካታ ማኅበረሰቦች የገንዘብ እና የቁሳቁስ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አቶ ክፍሌ አብራርተዋል፡፡
አክለውም ኮርፖሬሽኑ በ2016 በጀት ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን ከማስቀጠል ባሻገር ለተለያዩ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ከ16 ሚሊየን ብር በላይ ማውጣቱን ጠቁመው፣ ኮርፖሬሽኑ ከአከናወናቸው ሥራዎች አንዱ የወይዘሮ መክዳ አብዱራሂም መኖሪያ ቤት ግንባታ መሆኑን አስታውቀዋል።
በቀጣይም የኮርፖሬሽኑ የፋይናንስ አቅም እየታየ ተጨማሪ የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች ለማከናወን ጥረት እንደሚደረግ ቃል ገብተዋል። በኮርፖሬሽኑ የውስጥ አቅም በ885 ሺህ 197 ብር ወጪ በ63 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የተገነባው የወይዘሮ መክዳ መኖሪያ ቤት በብሎኬት የተሰራ ሲሆን፣ ከተገነባ 48 ዓመታት ሞልቶት የነበረውን የቀድሞውን አሮጌ ቤት አፍርሶ ለመገንባት 55 ቀናት ወስዷል፡፡ በአዲስ መልክ የተገነባው ይህ መኖሪያ ቤት ሳሎን እና ሁለት የመኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፣ የቤት ውስጥ ቁሳቁስም ተሟልቶለታል፡፡ በሀገር ሽማግሌዎች እና በአባ ገዳዎች ምርቃት የተጀመረው የዕለቱ የምረቃ እና የቁልፍ ርክክብ ሥነ ሥርዓት የሮቤ ከተማ አስተዳደር የበሃቢፍቱ ቀበሌ መስተዳድር ለኮርፖሬሽኑ የበላይ አመራሮች የጋቢ ሥጦታ አበርክቶ ተጠናቋል። በተመሳሳይ ዜና ኮርፖሬሽኑ በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ያስገነባውን ተጨማሪ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚያስመርቅ ይጠበቃል። ግብርናን ከማዘመን ጎን ለጎን ማኅበራዊ ኃላፊነታችንን በመወጣት ለሕዝብ ያለንን አጋርነት እናረጋግጣለን!
* የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ላይ ዘንድሮ የታየው አፈጻጸምም ጥሩ ነው ተብሏል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በመንግሥት የተሰጠውን ተልዕኮ እየተወጣ እና ትርፋማነቱን እያረጋገጠ በመዝለቁ ሊበረታታ እንደሚገባ በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
ይህ የተገለጸው የኮርፖሬሽኑ የ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በቀረበበት ወቅት ነው።
በዚሁ ወቅት የቋሚ ኮሚቴው የአገልግሎት ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ኢያሱ ሳላ እንደገለጹት፣ ኮርፖሬሽኑ በመላ ሀገሪቱ ምርትና አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ ከሚያከናውነው ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴ ባሻገር ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ቀጣይነት ያለው ትርፍ እያረጋገጠ መሄዱ የሚያበረታታ ተግባር ነው ብለዋል።
ሰብሳቢው አክለውም ኮርፖሬሽኑ በዘጠኝ ወራት ያሳካቸውን የልማት ሥራዎች እንዲያስጠብቅ እንዲሁም የተጀመሩ ሥራዎችን በማሳካት እድገቱን እንዲያስቀጥል አሳስበዋል።
የፕሮጀክት አተገባበርን አስመልክተው በሰጡት አስተያየትም፣ ተቋሙ ለፕሮጀክት አፈጻጸም መሻሻል ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት ተናግረዋል።የቋሚ ኮሚቴው የኢንዱስትሪ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ አዲስ ዓለማየሁ በበኩላቸው፣ የኮርፖሬሽኑን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አድንቀው፣ ኮርፖሬሽኑ ምክር ቤቱ ድጋፍ እንዲያደርግለት ከጠየቃቸው ጉዳዮች ውስጥ አብዛኛዎቹ ላይ ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። ይሁንና ተሰብሳቢ ሒሳብ ላይ ግን ኮርፖሬሽኑ እራሱ ማስፈጸም እንዳለበት አስገንዝበዋል።የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ላይ ዘንድሮ የታየው አፈጻጸም ጥሩ ነው ያሉት ወ/ሮ አዲስ፣ ከዚህ ቀደም ማዳበሪያ ከውጭ ለማስገባት የሚያጋጥሙ የኤልሲ፣ የግዥ እና የሥርጭት ተግዳሮቶች አሁን ላይ እንደተፈቱ መረዳታቸውን ጠቁመዋል፡፡አስተያየታቸውን ሲያጠቃልሉም፣ የደን ውጤቶችን (ሙጫ፣ ዕጣን፣ ከርቤና አበከድ) ለመሰብሰብና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የሚደረገው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
በዕለቱ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም የተቋሙን አሁናዊ ቁመና፤ የ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም፤ የ2013፣ 2014 እና 2015 በጀት ዓመታት ነቀፌታ የሌላቸው የኦዲት ግኝቶች (Unqualified audit opinion)፤ የፕሮጀክቶችና ካፒታል ግዥዎች ዕቅድ አፈጻጸም እንዲሁም ድጋፍና ክትትል የሚሹ ጉዳዮችን በሪፖርት መልክ ለቋሚ ኮሚቴው አቅርበዋል።በመጨረሻም በቋሚ ኮሚቴው ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽ ሰጥተዋል።
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!
የግብርና ግብዓቶችን እና የእርሻ መሣሪያዎችን ከተቀጽላቸውና መለዋወጫቸው ጋር በማቅረብ እንዲሁም ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ የሚዘልቅ የተቀናጀ የግብርና ሜካናይዜሽን አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው የአርሶና አርብቶ አደሩ አለኝታ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ከቻይና የእርሻ መሣሪያዎች እና የኮንስትራክሽን ማምረቻ ኩባንያዎች በቅርቡ የሚያስመጣቸው ዶዘሮች፣ ስካቬተር፣ ዎኪንግ ትራክተሮች እና የሩዝ መሰብሰቢያ ማሽን (Rice combine harvester)
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ጥሩ መሆኑን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ አስታወቀ።
በግብርና ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ ሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም የተገመገመው የኮርፖሬሽኑ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በአራቱ የውጤት ተኮር እይታዎች ሲመዘን ጥሩ እንደሆነ የቦርድ ሰብሳቢው ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
ሰብሳቢው በቀጣዮቹ ሁለት ወራት ከኮርፖሬሽኑ የተሻለ ውጤት እንደሚጠበቅ ገልጸው፣ በእነዚህ ጊዜያት የግብርና ግብዓቶችን በተሟላ ሁኔታ ለአርሶ አደሩ እና በግብርናው ዘርፍ ለተሰማሩ አካላት ለማቅረብ የቅርብ ክትትል ያስፈልጋል ብለዋል።
ቀጣዩ ጊዜ በግብርናው ዘርፍ ወቅታዊ ሥራዎች የሚከናወኑበት ወሳኝ ወቅት ነው ያሉት ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)፣ ይህንን ለማሳካት ኮርፖሬሽኑ ከክልሎች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመስራት በዘርፉ እንደ ሀገር የተያዙ ዕቅዶችን መፈጸም እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል።
ለዚህም ኮርፖሬሽኑ በዘጠኝ ወራት በከፊል የፈጸማቸውን የተወሰኑ ሥራዎች በቀጣዮቹ ሁለት ወራት ሙሉ በመሉ ለመተግበር ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ በአጽንዖት ተናግረዋል።
አክለውም የኮርፖሬሽኑ ማኔጅመንት የነገን ዛሬ ላይ በመስራት ተቋሙን በሁሉም የሥራ ዘርፎች ውጤታማ እና በገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ ማድረግ እንደሚጠበቅበት ነው ያሳሰቡት።በመጨረሻም ተቋሙ የኤክስፖርት አቅሙን ለማሳደግ የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኙ ምርቶች ላይ የበለጠ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት አበክረው አስገንዝበዋል።
በዕለቱ ከሥራ አመራር ቦርድ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም እና የማኔጅመንት አባላት ምላሽ ሰጥተዋል።
###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!
* The company shows interest in working with EABC to supply Granular Urea and buy Natural Gum
Addis Ababa, May 24, 2024 (EABC): The Ethiopian Agricultural Businesses Corporation’s (EABC) Chief Executive Officer has discussed with Chinese high level delegation from China Petroleum Technology and Development Corporation (CPTDC).
The Ethiopian Agricultural Businesses Corporation’s CEO, Kifle Woldemariam welcomed the officials of the company in his office and discussed with them; on May 24th, 2024.
During the discussion, the delegation of the Chinese company (CPTDC) shows interest in working with EABC to supply Granular Urea fertilizer and buy Natural Gum.The authorities of the company presented detailed information about the Granular Urea which they proposed to supply to EABC.For his part, Kifle, CEO of EABC discloses that the proposal will benefit EABC and CPTDC as well.
Furthermore, he announced that the purchase of the Granular Urea fertilizer will become effective when the price, quality and type of the fertilizer are approved by the Ministry of Agriculture of Ethiopia and the Board of Directors of EABC.Meanwhile, CPTDC has purchased natural gum from EABC through its sister company and it was also learned that the delegation is interested in buying up to 3000 metric tons per year.
China Petroleum Technology and Development Corporation (CPTDC) is established in 1987 and a wholly-owned subsidiary of China National Petroleum Corporation that mainly engages in the global trade of energy equipment, petrochemical products, industrial and civilian products.
The company is among the earliest state-owned enterprises in China to engage in global business.
###
Modernizing agriculture is our goal!
ግብርናን ለማዘመን እየሰራ የሚገኘው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ከተቋቋመበት ከታህሳስ 2008 ዓ.ም ጀምሮ ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ የሚዘልቅ የተቀናጀ የሜካናይዜሽን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
ከዚህ በተጨማሪ ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ግብዓቶችን እንዲሁም የእርሻ መሣሪያዎችን ከእነተቀጽላቸው እና መለዋወጫቸው ጋር በተመጣጣኝ ዋጋ ለደንበኞቹ በማቅረብ ላይ ነው።
በሌላ በኩል የእርሻ መሣሪያዎችን በከፊል በመገጣጠም፣ ዘር በማበጠር፣ የደረቅ ጭነት ትራንስፖርት በማመቻቸት እና ከሽያጭ በኋላ የቴክኒክና ሞያ፣ የምክርና የጥገና አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት እየተጋ የሚገኝ ተቋም ነው።
ኮርፖሬሽኑ የተፈጥሮ ሙጫ ምርቶችን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የሚያገኘውን የውጭ ምንዛሪ ለእርሻ መሣሪያዎች እና መለዋወጫዎች ግዥ መደጎሚያነትም ያውላል፡፡ኢግሥኮ ባለፉት ስምንት ዓመታት ተልእኮውን ለመወጣት በአደረገው ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ ችሏል።
በዚህም በየዓመቱ ገቢውን በማሳደግ ትርፋማ የሆነ የመንግሥት የልማት ድርጅት ነው።
በኦፕሬሽን ሥራዎች በግሉ ዘርፍና በተደራጁ ማኅበራት የማይሸፈኑ የገበያ ክፍተቶች ውስጥ የድርሻውን በማበርከት ላይ የሚገኘው ኮርፖሬሽኑ፣ ዓመታዊ ሽያጩን ሲቋቋም ከነበረበት 1.4 ቢሊዮን ብር በ2015 በጀት ዓመት ከ11.2 ቢሊዮን ብር በላይ ከፍ ማድረግ ችሏል፡፡
በተመሳሳይ ከታክስ በፊት ያለውን ትርፍ ከ45.6 ሚሊዮን ብር ወደ 1.5 ቢሊዮን ብር አሳድጓል፡፡
ይህ በመሆኑም ሲቋቋም በመንግሥት የተፈቀደለትን 2.44 ቢሊዮን ብር ካፒታል በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ በማሟላት አሁን ላይ ካፒታሉን ወደ 7 ቢሊዮን 564 ሚሊዮን ብር አድርሷል፡፡
በአጠቃላይ የአርሶና አርብቶ አደሩ አለኝታ የሆነው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) በአንድ መስኮት የተቀናጀ የሜካናይዜሽን አገልግሎት በመስጠት እንዲሁም ምርጥ ዘር፣ ጠጣርና ፈሳሽ ማዳበሪያዎች፣ አግሮኬሚካሎች፣ የእንስሳት መድሃኒት እና እርሻ መሣሪያዎች በማቅረብ ግብርናን ለማዘመን ከሚያደርገው ከፍተኛ ጥረት በተጨማሪ ማኅበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት ረገድ በሕዝብ ዘንድ ይታወቃል።
(አዲስ አበባ፣ ጥር 10 ቀን 2016 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) የግብርና ሚኒስትሩ ዶ/ር ግርማ አመንቴ እና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትሩ ዶ/ር ዓለሙ ስሜ በ2016/17 ምርት ዘመን የአፈር ማደበሪያ አገባብ ዕቅድ ክንውን ላይ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በተያዘው የምርት ዘመን የግብርና ሚኒስቴር 23 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት አቅዶ ከክልሎች በተሰበሰበው የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎት መሰረት 19.4 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት 930 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ተድርጎ ግዥ እየተፈጸመ መሆኑን ዶ/ር ግርማ አመንቴ ተናግረዋል፡፡ ግዥ ከተፈፀመው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥም 5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ ገብቷል ብለዋል ሚኒስትሩ፡፡ በምርት ዘመኑም ከሚገዛው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ 25 በመቶው ለመስኖ ስንዴ ልማት፣ 20 በመቶው ለበልግ እርሻ ስራ እንዲሁም ቀሪው 55 በመቶ ለመኸር እርሻ ጥቅም ላይ እንደሚውል አብራርተዋል፡፡ አርሶና አርብቶ አደሩም የሚቀርብለትን የአፈር ማዳበሪያ በአግባቡ በመጠቀም የግብርና ልማት ስራዎችን እንዲያከናውኑ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የአፈር ማዳበሪያ የማጓጓዙን ስራ ለማከናወን ከ10 ሺህ በላይ የየብስ ተሸከርካሪዎችን በማሰማራት እየተሰራ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ከ16 በላይ የባቡር ማጓጓዣዎችንም በመጠቀም ወደብ የደረሰውን የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ የማስገባት ስራ እየተሰራ መሆኑን ዶ/ር ዓለሙ ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም የ2016/17 በጀት ዓመት የአፈር ማደበሪያ አገባብ ዕቅድ እና ክንውን ላይ የስትሪንግ ኮሚቴ ውይይት ተካሂዷል፡፡
ካሜራ፡- ያሬድ አሰፋ
ዘጋቢ፥- ሰለሞን ደምሰው