የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

የኮካ እርሻ ልማት ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20/2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በምዕራብ ኦሞ ዞን ኮካ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የተረከበውን 5 ሺህ ሄክታር መሬት ለማልማት የሚያስችለውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራ ዛሬ ታህሳስ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀመረ።
በልማት ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል፣ የምዕራብ ኦሞ ዞን፣ የማጂና ሱሪ ወረዳዎች አመራሮች እንዲሁም የኮርፖሬሽኑ ተወካይ ተገኝተዋል።
ኮርፖሬሽኑ ኮካ ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ በተረከበው መሬት ምርጥ ዘር እንደሚያባዛ እና ወደ ውጭ የሚላኩ ሰብሎችን እንደሚያመርት መገለጹ ይታወሳል።
ሦስተኛ የልማት መዳረሻው ከሆነው የኮካ እርሻ መሬት ልማት በተጨማሪ በክልሉ የታማሻሎ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻ ልማት እና በቅርቡ እንደሚመረቅ የሚጠበቀውን የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓት እና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ፕሮጀክት እያስተዳደረ ይገኛል።
###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!

ኮርፖሬሽኑ በትግራይ ክልል በጦርነት ፈርሰው የነበሩ የመማሪያ ክፍሎችን ገንብቶ አስመረቀ

Czech Republic Deputy Prime Minister visits EABC

ኮርፖሬሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሦስተኛ የልማት መዳረሻውን ለማልማት መዘጋጀቱን አስታወቀ

ነገን አሻግሮ በማየት እና በጽናት የተገኘ ውጤት

Supply of 611,158 METRIC TON Granular DAP (Di ammonium phosphate) soil fertilizer and 821,371 METRIC TON Granular Urea soil fertilizer

አዲሶቹን የሲኖትራክ ሞዴሎች በቅርቡ ይጠብቁ!

ኮርፖሬሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በአከናወነው የግብርና ልማት እውቅና እያገኘ ነው

EABC receives walking tractors

በኮርፖሬሽኑ እና በሠራተኛ ማኅበር መካከል የኅብረት ስምምነት ተፈረመ