የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

EABC earns 846 thousand USD from exporting incense & gum

ኮርፖሬሽኑ ከእጣን እና ሙጫ 846 ሺህ የአሜሪካን ዶላር አገኘ

ኮርፖሬሽኑ በአፈር ማዳበሪያ ግዥ፣ አቅርቦትና ሥርጭት መሳለጥ ለአበረከተው የጎላ አስተዋጽዖ ተሸለመ

አቶ ሰለሞን ገብሬ
የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ

ለመስኖ እርሻ የሚውል የአፈር ማዳበሪያ የግዥ ሂደት ተጀመረ

Ethiopian Investment Holdings’ CEO congratulates EABC staff on their successful achievements of 2016 fiscal year

“ኮርፖሬሽኑ በ2016 በጀት ዓመት ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገቡ እንኳን ደስ ያላችሁ” የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ

“ተቋሙ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዋልታ በመሆኑ ቦርዱ የሚጠበቅበትን ሁሉ ያደርጋል” የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባል

በ2016 እቅድ አፈጻጸም እና በ2017 እቅድ ዙሪያ ውይይት ተደረገ

የኮርፖሬሽኑ የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ጥሩ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ገለጸ

የኮርፖሬሽኑ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ሻራቸውን አኖሩ

5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ ገብቷል – ዶክተር ግርማ አመንቴ

(አዲስ አበባ፣ ጥር 10 ቀን 2016 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) የግብርና ሚኒስትሩ ዶ/ር ግርማ አመንቴ እና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትሩ ዶ/ር ዓለሙ ስሜ በ2016/17 ምርት ዘመን የአፈር ማደበሪያ አገባብ ዕቅድ ክንውን ላይ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በተያዘው የምርት ዘመን የግብርና ሚኒስቴር 23 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት አቅዶ ከክልሎች በተሰበሰበው የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎት መሰረት 19.4 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት 930 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ተድርጎ ግዥ እየተፈጸመ መሆኑን ዶ/ር ግርማ አመንቴ ተናግረዋል፡፡ ግዥ ከተፈፀመው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥም 5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ ገብቷል ብለዋል ሚኒስትሩ፡፡ በምርት ዘመኑም ከሚገዛው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ 25 በመቶው ለመስኖ ስንዴ ልማት፣ 20 በመቶው ለበልግ እርሻ ስራ እንዲሁም ቀሪው 55 በመቶ ለመኸር እርሻ ጥቅም ላይ እንደሚውል አብራርተዋል፡፡ አርሶና አርብቶ አደሩም የሚቀርብለትን የአፈር ማዳበሪያ በአግባቡ በመጠቀም የግብርና ልማት ስራዎችን እንዲያከናውኑ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የአፈር ማዳበሪያ የማጓጓዙን ስራ ለማከናወን ከ10 ሺህ በላይ የየብስ ተሸከርካሪዎችን በማሰማራት እየተሰራ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ከ16 በላይ የባቡር ማጓጓዣዎችንም በመጠቀም ወደብ የደረሰውን የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ የማስገባት ስራ እየተሰራ መሆኑን ዶ/ር ዓለሙ ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም የ2016/17 በጀት ዓመት የአፈር ማደበሪያ አገባብ ዕቅድ እና ክንውን ላይ የስትሪንግ ኮሚቴ ውይይት ተካሂዷል፡፡
ካሜራ፡- ያሬድ አሰፋ
ዘጋቢ፥- ሰለሞን ደምሰው