የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

ኮርፖሬሽኑ በትራክተር የሚጎተቱ ጣልያን ሰራሽ የኬሚካል መርጫ ማሽኖችን አስመጣ

ከቻይናው ዙምላይን የገዛቸው ኮምባይን ሀርቨስተሮችም ጂቡቲ ወደብ ደርሰዋል
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 19/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):-የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) በትራክተር የሚጎተቱ 15 ጣልያን ሰራሽ የኬሚካል መርጫ ማሽኖችን በ425 ሺህ 280 የአሜሪካን ዶላር (23 ሚሊዮን 605 ሺህ 251.456 ብር) አስመጣ።
በእርሻ መሣሪያዎች እና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ የእርሻ መሣሪያዎች አቅርቦት፣ ማርኬቲንግና ሽያጭ መምሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ቶሎሳ እንዳስታወቁት፣ እያንዳንዱ ማሽን 3 ሺህ ሊትር አግሮኬሚካሎችን የመያዝ አቅም አለው።አክለውም ማሽኖቹ 24 ሜትር ስፋት እና ቁመታቸውም እስከ 2 ሜትር ከፍ እንደሚል ገልጸዋል።በሌላ ዜና ኮርፖሬሽኑ ከቻይናው ዙምላይን የእርሻ መሣርያ አምራች ኩባንያ ጋር ሰኔ 25/2015 ዓ.ም በገባው የንግድ ስምምነት መሰረት የገዛቸው 10 ኮምባይን ሀርቨስተሮች ጂቡቲ ወደብ መድረሳቸውን አቶ ጎሳ ተናግረዋል።ኮምባይን ሀርቨስተሮቹ በ648 ሺህ 600 የአሜሪካን ዶላር (36 ሚሊዮን 672 ሺህ 72 ብር) መገዛታቸውን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ፣ በቅርቡ ወደ ሀገር ውስጥ ተጓጉዘው ለ2015/16 የምርት ዘመን የአጨዳ ሥራ እንደሚደርሱ አስታውቀዋል።

Spare Part Supply