- ኮርፖሬሽኑ በ20 ሺህ ሔክታር ላይ የደረሱ የምርጥ ዘር ሰብሎችን እየሰበሰበ ነውአዲስ አበባ፤ ሕዳር 3/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ20 ሺህ ሔክታር ላይ የደረሱ የምርጥ ዘር ሰብሎችን እየሰበሰበ መሆኑን አስታወቀ። የኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽንና ማኅበራዊ ኃላፊነት ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ ጋሻው አይችሉህም ለኢዜአ እንዳሉት፥ ተቋሙ በራሱ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻዎች እንዲሁም በኮንትራት ዘር አባዥ እርሻ (በሰፋፊ የባለሃብቶች እርሻ)፣ በክላስተር በተደራጁ አርሶ አደሮች ማሳ እና በሦስት የግብርና ቴክኒክና ሞያ ትምህርት ሥልጠና ኮሌጆች እርሻ… Read more: ኮርፖሬሽኑ በ20 ሺህ ሔክታር ላይ የደረሱ የምርጥ ዘር ሰብሎችን እየሰበሰበ ነው
- ዉግዛል/WUXALማክሮሚክስ ፈሳሽ ማዳበሪያ – የሁሉ ምርጫየኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) በዋና መ/ቤቱ እና በክልሎች በሚገኙ ቅርንጫፎቹ ለአርሶ አደሮች፣ ከፊል አርብቶ አደሮች እና ባለሃብቶች ከሚያከፋፍላቸው የግብርና ግብዓቶች አንዱ ዉግዛል/WUXAL ነው። ዉግዛል/WUXALማክሮሚክስ ፈሳሽ ማዳበሪያ በሰብል፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ቅጠል ላይ የሚረጭ ሲሆን፣ የምርት ጥራትና ምርታማነት እንዲጨምር ያግዛል፤ የሰብሎችን በሽታ የመቋቋም አቅምም ያሳድጋል። ምን ይሄ ብቻ፤ ምርትን በአጭር ጊዜ፣ በከፍተኛ መጠንና ጥራት ለማምረት እንዲሁም የአፈር ብክለትና የማዳበሪያ ንጥረ ነገር… Read more: ዉግዛል/WUXALማክሮሚክስ ፈሳሽ ማዳበሪያ – የሁሉ ምርጫ
- ዱዝ-ፋር (DEUTZ-FAHR) ትራክተር – የአውሮፓ ስሪትየኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ለኢትዮጵያ የአየር ንብረትና የመሬት አቀማመጥ ተስማሚ የሆነውን ዱዝ-ፋር ትራክተር በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች በድጋሚ ማቅረቡን ሲገልጽ በደስታ ነው። ወደ ኮርፖሬሽናችን ጎራ ሲሉ ከእርሻ መሣሪያዎች በተጨማሪ አረም፣ ተባይ፣ የሰብል በሽታና የመጋዘን ነፍሳትን ጥርግርግ አድርገው የሚያጠፉ አንጀት አርስ የአግሮኬሚካሎች ቡፌ /buffet/ በአይነት በአይነቱ ያገኛሉ። ይምጡ! በአገልግሎታችን ተደስተው ይመለሳሉ። ለበለጠ መረጃ :- ለትራክተርና ለእርሻ መሣሪያዎች መለዋወጫ 0114 – 423… Read more: ዱዝ-ፋር (DEUTZ-FAHR) ትራክተር – የአውሮፓ ስሪት
- ብሔራዊ ጥቅም እና የጂኦስትራቴጂ ቁመና” ርዕሰ ጉዳይ ላይ ውይይት ተደረገአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7/2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- “ብሔራዊ ጥቅም እና የጂኦስትራቴጂ ቁመና” ርዕሰ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ተወያዩ። በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት የተካሄደውን የውይይት መድረክ የመሩት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺእመቤት ነጋሽ በ”ብሔራዊ ጥቅምና የጂኦስትራቴጂ ቁመና” ርዕሰ ጉዳይ ላይ የተዘጋጀን የመነሻ ሰነድ አቅርበዋል። ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ በዚህ ወቅት ባደረጉት ገለጻ፣ ብሔራዊ… Read more: ብሔራዊ ጥቅም እና የጂኦስትራቴጂ ቁመና” ርዕሰ ጉዳይ ላይ ውይይት ተደረገ
- የአርሶ አደሮች የመስክ ቀንበሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስተባባሪነት BH-520 እና BH-549 ድቃይ በቆሎ ለአርሶ አደሮችና ለግብርና ባለሞያዎች የማስተዋወቅ ሥራ – በሲዳማ ክልል ቦና ወረዳ
- የኢግሥኮ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻዎችና የሰብል ምርት በከፊልየኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) በቅድመ መስራች፣ መስራች እና የተመሰከረለት ዘር ደረጃዎች የ22 ሰብሎችን 91 ዝርያዎች በእራሱ እርሻዎች እንዲሁም በባለሃብቶች ሰፋፊ እርሻዎችና በአርሶ አደሮች ማሳ በሽርክና እያባዛ ይገኛል።
- የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከሠራተኛ ማኅበር አመራሮችና ከመላ ሠራተኞች ጋር ተወያዩአዲስ አበባ፣ መስከረም 21/2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከተቋሙ የሠራተኛ ማኅበር አመራሮችና ከመላ ሠራተኞች ጋር መስከረም 21/2018 ዓ.ም ተወያዩ። ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ወይዘሮ የሺእመቤት ነጋሽ በዛሬው ዕለት በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት በተዘጋጁ ሁለት የትውውቅና የውይይት መድረኮች ላይ ባስተላለፉት መልእክት፣ ኮርፖሬሽኑን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ከሠራተኛ ማኅበር አመራሮች እንዲሁም ከመላ ሠራተኞች ጋር ተቀራርበው በጋራ እንደሚሠሩ ተናግረዋል። በመተማመንና ተቀራርቦ… Read more: የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከሠራተኛ ማኅበር አመራሮችና ከመላ ሠራተኞች ጋር ተወያዩ
- የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከተቋሙ የሥራ አመራር ጋር ተዋወቁአዲስ አበባ፣ መስከረም 20/2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከተቋሙ የሥራ አመራር ጋር ትውውቅ አደረጉ። ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ወይዘሮ የሺእመቤት ነጋሽ መስከረም 20/2018 ዓ.ም በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ተገኝተው ከሥራ አመራሩ ጋር ተዋውቀዋል። በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፣ ኮርፖሬሽኑ ግብርናን በማዘመንና የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደተጣለበት አስታውቀው፣ በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩና አዳዲስ የልማት ሥራዎችን በጋራ ጥረት ይበልጥ… Read more: የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከተቋሙ የሥራ አመራር ጋር ተዋወቁ
- Board Appoints Yeshiemebet Negash as EABC CEOAddis Ababa, October 2, 2025 (EABC): The Ethiopian Agricultural Businesses Corporation (EABC) Board of Directors has appointed Yeshiemebet Negash as Chief Executive Officer of the Corporation, effective September 26, 2025. Yeshiemebet previously served as CEO of the Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise (EIIDE) for more than five years, from April 2020 to September 25, 2025. She is currently a member… Read more: Board Appoints Yeshiemebet Negash as EABC CEO
- ወይዘሮ የሺእመቤት ነጋሽ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተመደቡአዲስ አበባ፣ መስከረም 20/2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ሥራ አመራር ቦርድ ወይዘሮ የሺእመቤት ነጋሽ ከመስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እንዲሠሩ መድቧል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንደስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅትን (ኢኢግልድ) ከሚያዝያ 2012 ዓ.ም እስከ መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ከአምስት ዓመታት በላይ ያስተዳደሩት ወይዘሮ የሺእመቤት ነጋሽ፣ ከመስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም… Read more: ወይዘሮ የሺእመቤት ነጋሽ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተመደቡ
- የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ በአዲስ መልክ ተደራጀአዲስ አበባ፣ መስከረም 15/2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ለኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን መስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም በጻፈው ደብዳቤ እንዳሳወቀው፣ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ አመራር ቦርድ በአዲስ መልክ ተደራጅቷል። በዚህ መሰረት ከመስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ:- ክብርት ወ/ሮ ዓለምፀሀይ ጳውሎስ – የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር – የቦርድ ሰብሳቢ ክቡር አቶ አዲሱ አረጋ – የኢፌዴሪ… Read more: የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ በአዲስ መልክ ተደራጀ
- የኮርፖሬሽኑ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ* በ2018 በጀት ዓመት ካለፉት ዓመታት የላቀ ውጤት ማምጣት እንደሚጠበቅበትም ተገልጿል አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (ኢኢሆ) አስታወቀ። የኮርፖሬሽኑ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ነሐሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በግዮን ሆቴል በተገመገመበት ወቅት ኮርፖሬሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ያስመዘገበው አፈጻጸም ከፍተኛ… Read more: የኮርፖሬሽኑ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ
- የኢግሥኮ በረከቶችየኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በቅድመ መስራች፣ መስራች እና የተመሰከረለት ዘር ደረጃዎች የ22 ሰብሎችን 91 ዝርያዎች በእራሱ እርሻዎች እንዲሁም በባለሃብቶች ሰፋፊ እርሻዎችና በአርሶ አደሮች ማሳ በሽርክና እያባዛ ይገኛል።በዚህ መሰረት የኮርፖሬሽኑ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻዎች እና የፍራፍሬና የቡና ማሳዎች አሁናዊ ገጽታ በከፊል የሚከተለውን ይመስላል።ስንዴ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ሩዝ፣ አኩሪ አተር፣ ባቄላ፣ ተልባ፣ ጎመንዘር፣ ቡና፣ ብርቱካን፣ ፓፓያ ይቀጥላል … ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!
- የኮርፖሬሽኑ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ገለጸየኮርፖሬሽኑ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ገለጸአዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 21/2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ገለጸ።ቦርዱ ይህን የገለጸው፣ በግብርና ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ ሚያዝያ 21 ቀን 2017 ዓ.ም የኮርፖሬሽኑ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት ነው።በዚሁ ወቅት የግብርና ሚኒስትር እና የኮርፖሬሽኑ የቦርድ… Read more: የኮርፖሬሽኑ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ገለጸ
- ማስታወቂያለኢትዮጵያ የግብርና ልማት ተስማሚ የሆኑ የእርሻ መሣሪያዎች እና የግብርና ግብዓቶች – ከኢግሥኮ ሁሌም ሙሉ፣ ዘወትርም ዝግጁ ሆኖ ወደሚጠብቅዎ የአርሶና አርብቶ አደሩ አለኝታ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ጎራ ይበሉና ለእርስዎ የንግድና የልማት ሥራዎች ይስማማሉ ብለን ያቀረብናቸውን ትራክተሮች፣ ኮምባይን ሀርቨስተሮች፣ ማረሻዎች፣ መከስከሻዎች፣ መስመር ማውጫዎች፣ ኬሚካል መርጫ ማሽኖች፣ የእርሻና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች መለዋወጫዎች፣ ጎማዎች፣ ባትሪዎች፣ ፊልትሮዎች፣ አግሮኬሚካሎች፣ ፈሳሽ ማዳበሪያዎች ወዘተ በተመጣጣኝ ዋጋ ገዝተው… Read more: ማስታወቂያ
- የኮርፖሬሽኑን ልማት ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁአሶሳ፣ መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እያካሄደ የሚገኘውን የልማት ሥራ ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን የክልሉ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን አስታወቁ።ርዕሰ መስተዳድሩ ይህንን ያስታወቁት፣ በኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም የተመራ የልዑካን ቡድን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በአነጋገሩበት ወቅት ነው። ውይይቱ በዋነኛነት ያተኮረው ኮርፖሬሽኑ ለክልሉ ባቀረበው የበቆሎ ምርጥ ዘር ማባዣ የእርሻ መሬት ጥያቄ… Read more: የኮርፖሬሽኑን ልማት ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ
- ማስታወቂያ 130፣ 145 እና 165 የፈረስ ጉልበት ያላቸው ጣልያን ሰራሽ ዱዝ-ፋር (DEUTZ-FAHR) ትራክተሮች በድጋሚ ለገበያ ቀረቡ * ባለ 180 የፈረስ ጉልበት እየመጣ ነው
- ማስታወቂያክቡራን ደንበኞቻችን፣የአርሶና አርብቶ አደሩ አለኝታ የሆነው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት አዲስ አበባ በሚገኘው ዋና መ/ቤት ከሰኞ እስከ አርብ ከሚሰጠው መደበኛ አገልግሎት በተጨማሪ ከነገ ቅዳሜ መጋቢት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወር ሁለት ቅዳሜ ቀናትን ቢሮዎቹን ክፍት በማድረግ ሊያገለግላችሁ መዘጋጀቱን ሲገልጽ በታላቅ ደስታ ነው።በዚህ መሰረት:- መጋቢት 6፣ መጋቢት 20፣ ሚያዝያ… Read more: ማስታወቂያ
- ለክቡራን ደንበኞቻችን የቀረቡ የአውሮፓ ስሪት የኬሚካል መርጫ መሣሪያዎችከአውሮፓ በአስመጣቸው ‘ዱዝ-ፋር’ እና ‘ዜቶር’ ትራክተሮች በደንበኞቹ ዘንድ ምስጋና እና አድናቆት የተቸረው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ)፣ እነሆ የገበያውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ በትራክተር የሚጎተቱ 3 ሺህ ሊትር አግሮኬሚካል የመያዝ አቅም ያላቸውን ጣልያን ሰራሽ ማሽኖች በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረቡን ሲገልጽ፣ ጥራት ላይ በመተማመን ነው። የጣልያኑ ሶጅማ ኩባንያ ምርት የሆኑት እነዚህ የኬሚካል መርጫ መሣሪያዎች 24 ሜትር ስፋት ያላቸው ሲሆን፣ ቁመታቸው እስከ 2 ሜትር… Read more: ለክቡራን ደንበኞቻችን የቀረቡ የአውሮፓ ስሪት የኬሚካል መርጫ መሣሪያዎች
- የቼክ ሪፐብሊክ ‘ዜቶር (ZETOR)’ ትራክተሮች ዛሬም በገበያ ላይ ናቸውከጣልያኑ ዱዝ-ፋር ትራክተር በተጨማሪ 110፣ 120 እና 136 የፈረስ ጉልበት ያላቸውን ‘ዜቶር’ በመባል የሚታወቁ የቼክ ሪፐብሊክ ታዋቂ ትራክተሮችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች አቅርቧል።ይሄም ብቻ አይደለም፤ ወደ ተቋማችን ጎራ ሲሉ ሌሎች ትርፋማ የሚያደርግዎትን ማረሻ፣ መከስከሻ፣ መስመር ዋውጫ፣ ኬሚካል መርጫ፣ ዘር መዝሪያ፣ ማዳበሪያ መበተኛ፣ የእርሻ መሣሪያዎችና የከባድ ተሽከርካሪዎች ጎማ፣ ባትሪ እና ፊልትሮ በተመጣጣኝ ዋጋ፣ በጥራትና በብዛት ያገኛሉ።ለበለጠ መረጃ :- 0911 157091 ወይም 0114… Read more: የቼክ ሪፐብሊክ ‘ዜቶር (ZETOR)’ ትራክተሮች ዛሬም በገበያ ላይ ናቸው
- ዉግዛል/WUXALማክሮሚክስ ፈሳሽ ማዳበሪያ – በግብርና ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮች፣ ከፊል አርብቶ አደሮች እና ባለሃብቶች ምርጫበዋና መ/ቤት እና በክልሎች ባሉት 25 ቅርንጫፎች ለአርሶ አደሮች፣ ከፊል አርብቶ አደሮች እና ባለሃብቶች እያከፋፈለ የሚገኘው ዉግዛል/WUXALማክሮሚክስ ፈሳሽ ማዳበሪያ በሰብል፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ቅጠል ላይ የሚረጭ ነው።ዉግዛል/WUXAL የምርት ጥራት እና ምርታማነት እንዲጨምር ከማገዙ ባሻገር የሰብሎች በሽታን የመቋቋም አቅም እንዲያድግ ያስችላል፡፡ ምን ይሄ ብቻ፤ ምርትን በአጭር ጊዜ፣ በከፍተኛ መጠንና ጥራት ለማምረት እንዲሁም የአፈር ብክለትና የማዳበሪያ ንጥረ ነገር ትነት መጠንን ለመቀነስም ይጠቅማል።አግሉኮን በተባለ… Read more: ዉግዛል/WUXALማክሮሚክስ ፈሳሽ ማዳበሪያ – በግብርና ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮች፣ ከፊል አርብቶ አደሮች እና ባለሃብቶች ምርጫ
- EABC & EIH Sign Shareholders Agreement with Asset Green CompanyThe Agreement focuses on a transformative integrated dairy and crop farming project Addis Ababa, February 17, 2025 (EABC): Ethiopian Agricultural Businesses Corporation (EABC) and Ethiopian Investment Holdings (EIH) have signed a Shareholders Agreement with a foreign company, Asset Green, to collaborate on a transformative integrated dairy and crop farming project. The agreement was signed on February 17, 2025.The project to… Read more: EABC & EIH Sign Shareholders Agreement with Asset Green Company
- Bonga Integrated Agricultural Input and Mechanization Service CenterThe Integrated Agricultural Input and Mechanization Service Center, built by the Ethiopian Agricultural Businesses Corporation in Bonga City, was inaugurated last Saturday, February 8, 2025 and has officially commenced its services. Here is a brief description of the project. The Ethiopian Agricultural Businesses Corporation (EABC) is a public enterprise that has practically proven itself as a beacon of hope for… Read more: Bonga Integrated Agricultural Input and Mechanization Service Center
- ኮርፖሬሽኑ በቦንጋ ያስገነባው የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ተመረቀ* “ማዕከሉ የደበብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መሰረታዊ ችግር የነበረውን የግብርና ግብዓት አቅርቦት በዘላቂነት ለመፍታት ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል” የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢንጂነር)* “ማዕከሉ ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብቻ ሳይሆን ለሌሎች አጎራባች ክልሎች እና ዞኖች ጭምር አገልግሎት እንዲሰጥ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ ነው።” የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) አዲስ አበባ፣ የካቲት 1/2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን… Read more: ኮርፖሬሽኑ በቦንጋ ያስገነባው የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ተመረቀ
- ኮርፖሬሽኑ በጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት እውቅና አገኘአዲስ አበባ፣ ጥር 28/2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት እውቅና አገኘ፡፡በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም በተዘጋጀ የእውቅና መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር መዓዛ አበራ (ኢንጂነር) የእውቅና የምስክር ወረቀቱን ለኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም አስረክበዋል፡፡ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር መዓዛ አበራ (ኢንጂነር) በበኩላቸው፣… Read more: ኮርፖሬሽኑ በጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት እውቅና አገኘ
- የኮርፖሬሽኑ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አበረታች መሆኑ ተገለጸ* “የኮርፖሬሽኑ የ2016 በጀት ዓመት የሂሳብ ሪፖርት ነቀፌታ የሌለበት (Unqualified Audit Opinion/Clean Audit Report) በመሆኑ የተቋሙ ማኔጅመንት ሊመሰገን ይገባል።” የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አዲስ አበባ፣ ጥር 12/2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ገለጸ። በግብርና ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ ጥር 12 ቀን 2017 ዓ.ም የተገመገመው የኮርፖሬሽኑ የመጀመሪያ… Read more: የኮርፖሬሽኑ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አበረታች መሆኑ ተገለጸ
- የኮካ እርሻ ልማት ተጀመረአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20/2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በምዕራብ ኦሞ ዞን ኮካ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የተረከበውን 5 ሺህ ሄክታር መሬት ለማልማት የሚያስችለውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራ ዛሬ ታህሳስ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀመረ።በልማት ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል፣ የምዕራብ ኦሞ ዞን፣ የማጂና ሱሪ ወረዳዎች አመራሮች እንዲሁም የኮርፖሬሽኑ ተወካይ ተገኝተዋል።ኮርፖሬሽኑ ኮካ… Read more: የኮካ እርሻ ልማት ተጀመረ
- ኮርፖሬሽኑ በትግራይ ክልል በጦርነት ፈርሰው የነበሩ የመማሪያ ክፍሎችን ገንብቶ አስመረቀ* “ኮርፖሬሽኑ ክልሉን ለመደገፍ ቀድሞ የተገኘ ተቋም በመሆኑ ሊመሰገን ይገባል” የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የትምህርት ቢሮ ኃላፊአክሱም፣ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በትግራይ ክልል ማዕከላዊ ዞን በጦርነት ፈርሰው የነበሩ የውቅሮ ማራይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የመማሪያ ክፍሎችን በ7.5 ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ አስገንብቶ እና የውስጥ ቁሳቁስ አሟልቶ ታህሳስ 11 ቀን 2017 ዓ.ም አስመረቀ። በምረቃ እና ርክክብ መርሐ ግብሩ… Read more: ኮርፖሬሽኑ በትግራይ ክልል በጦርነት ፈርሰው የነበሩ የመማሪያ ክፍሎችን ገንብቶ አስመረቀ
- Czech Republic Deputy Prime Minister visits EABCAddis Ababa, December 8, 2024 (EABC): A delegation led by Czech Republic Deputy Prime Minister, paid a visit to Ethiopian Agricultural Businesses Corporation (EABC) on December 8, 2024. Deputy Prime Minister Mr. Marian Jurečka and his delegation visited the Corporation’s Farm Machinery Maintenance and Assembly Workshop as well as Spare Parts Warehouse. Mr. Marian Jurečka welcomed by Girma Amentie (PhD), Minister… Read more: Czech Republic Deputy Prime Minister visits EABC
- ኮርፖሬሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሦስተኛ የልማት መዳረሻውን ለማልማት መዘጋጀቱን አስታወቀ* “ተቋሙ ወደ ምዕራብ ኦሞ ዞን ይዞት የመጣው ዕድል አምልጦን ትውልድ እንዳይወቅሰን መጠንቀቅ አለብን” የክልሉ የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ * “መከላከያ ሠራዊት ከክልሉ የፀጥታ ኃይል እና ከማኅበረሰቡ ጋር በመሆን ለአካባቢው ዘላቂ ሰላም እና ልማት በጋራ እየሰራ ይገኛል።” ጄነራል አስራት ዴኔሮ * “እስከዛሬ ሳናውቅ በልማት ወደ ኋላ በመቅረታችን ተጎድተናል፤ አሁን ግን ኮርፖሬሽኑ ይዞ የመጣው የልማት ዕድል ሊያመልጠን አይገባም።” የምዕራብ… Read more: ኮርፖሬሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሦስተኛ የልማት መዳረሻውን ለማልማት መዘጋጀቱን አስታወቀ
- ነገን አሻግሮ በማየት እና በጽናት የተገኘ ውጤትበቅርቡ እንደሚመረቅ የሚጠበቀው የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓት እና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ከብዙ በጥቂቱ የሚመለከተውን ይመስላል።
- አዲሶቹን የሲኖትራክ ሞዴሎች በቅርቡ ይጠብቁ!የግብርና ግብዓቶችን፣ የእርሻ እና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች እያቀረበ የሚገኘው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በቅርቡ አዳዲስ የሲኖትራክ ሞዴሎችን ሊያስመጣ መሆኑን ሲያበስርዎ በታላቅ ደስታ ነው። ምንጊዜም ለቃላችን ታማኝ መሆናችንን ደንበኞቻችን ምስክሮች ናቸው። እንደተለመደው ዋስትናውን እኛ ላይ ጥለው፣ እርስዎ አዳዲሶቹን ሞዴሎች ለመግዛት እና ትርፋማ ለመሆን ይዘጋጁ! Stay tuned for the latest Sinotruk models, coming soon! We are so much excited to… Read more: አዲሶቹን የሲኖትራክ ሞዴሎች በቅርቡ ይጠብቁ!
- ኮርፖሬሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በአከናወነው የግብርና ልማት እውቅና እያገኘ ነው“ኮርፖሬሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በአከናወነው የግብርና ልማት እውቅና እያገኘ ነው” የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አዲስ አበባ፣ ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በአጭር ጊዜ ውስጥ በአከናወነው የግብርና ልማት ሥራዎች እውቅና እያገኘ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ገለጹ፡፡ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ አቶ ማስረሻ በላቸው ይህንን የገለጹት፣ ኮርፖሬሽኑ… Read more: ኮርፖሬሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በአከናወነው የግብርና ልማት እውቅና እያገኘ ነው
- EABC receives walking tractorsAddis Ababa, November 12, 2024 (EABC): Ethiopian Agricultural Businesses Corporation (EABC) received walking tractors from Chenese Company, SIFANG on November 12, 2024.During the Handover Ceremony of the walking tractors, Mr. Xu, the General Manager of SIFANG, delivered the tractors to CEO of EABC, Kifle Woldemariam. After receiving tractors, Kifle made a remark that the SIFANG’s walking tractor is designed to… Read more: EABC receives walking tractors
- በኮርፖሬሽኑ እና በሠራተኛ ማኅበር መካከል የኅብረት ስምምነት ተፈረመአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን እና በተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማኅበር መካከል ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም 4ኛው የኅብረት ስምምነት ተፈረመ። በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም በአስተላለፉት መልእክት፣ ለቀጣይ ሦስት ዓመታት የሚቆየው ይህ የኅብረት ስምምነት ሁለቱ ተደራዳሪ አካላት ተቀራርበው በመስራታቸው ለውጤት በቅቷል ብለዋል። የስምምነቱ ዓላማ የሠራተኛውን የሥራ… Read more: በኮርፖሬሽኑ እና በሠራተኛ ማኅበር መካከል የኅብረት ስምምነት ተፈረመ
- ከአፈር ማዳበሪያ አቅራቢዎች ጋር ውይይት ተደረገአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡-የአፈር ማዳበሪያን በወቅቱ ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ በሚያስችል አሠራር ላይ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአፈር ማዳበሪያ አቅራቢዎች ጋር ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም በኮርፖሬሽኑ ዋና መስሪያ ቤት ውይይት አደረገ፡፡ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም፣ የውይይት መድረኩ ዓላማ በአፈር ማዳበሪያ ግዥ፣ ጨረታ፣ ትራንስፖርት እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ የጋራ መፍትሔ ማስቀመጥ መሆኑን አስረድተዋል።… Read more: ከአፈር ማዳበሪያ አቅራቢዎች ጋር ውይይት ተደረገ
- የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የልዑካን ቡድን የኮርፖሬሽኑን የምርጥ ዘር እርሻዎች ጎበኘ“የኮርፖሬሽኑ አምባሳደር በመሆን አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርጋለን” ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) የኢኢሆ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ============================= ሀዋሳ፣ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (ኢኢሆ) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) የሚመራ የልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻዎችን ጎበኘ። የልዑካን ቡድኑ ኮርፖሬሽኑ የሚያስተዳድራቸውን የጎንዴ እና አርዳይታ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻዎች እንዲሁም የኮፈሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዘር ዝግጅትን… Read more: የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የልዑካን ቡድን የኮርፖሬሽኑን የምርጥ ዘር እርሻዎች ጎበኘ
- ኮርፖሬሽኑ የታማኝ ግብር ከፋይነት የፕላቲነም ደረጃ ሽልማት ተበረከተለትኮርፖሬሽኑ የታማኝ ግብር ከፋይነት የፕላቲነም ደረጃ ሽልማት ተበረከተለት * በ2016 በጀት ዓመት ከ743 ሚሊየን ብር በላይ ግብር በመክፈል ለሁለተኛ ጊዜ በፕላቲነም ደረጃ ለመሸለም በቅቷል **** አዲስ አበባ፣ መስከረም 30/2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የታማኝ ግብር ከፋይነት የፕላቲነም ደረጃ ሽልማት ተበረከተለት። መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም በተካሄደ 6ኛው ዙር የ2016 የታማኝ ግብር ከፋዮች የምስጋና እና የእውቅና መርሐ ግብር ላይ… Read more: ኮርፖሬሽኑ የታማኝ ግብር ከፋይነት የፕላቲነም ደረጃ ሽልማት ተበረከተለት
- ኮርፖሬሽኑ ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ ድረስ አገልግሎት የሚሰጡ ዎኪንግ ትራክተሮችን አስመጣ* ለተጠቃሚዎች የሚሰጠውን የአዲስ እርሻ መሬት ዝግጅት አገልግሎት ለማስፋትም ዶዘሮች እና ኤክስካቬተር አስገብቷልአዲስ አበባ፣ መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ ድረስ የሜካናይዜሽን አገልግሎት የሚሰጡ ዎኪንግ ትራክተሮችን አስመጣ፡፡20 የፈረስ ጉልበት ያላቸው እነዚህ ትራክተሮች የቻይና ስሪት ሲሆኑ፣ በኮርፖሬሽኑ ባለሞያዎች ተገጣጥመዋል፡፡የኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎች አቅርቦት እና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ ክፍሌ እንደገለጹት፣ ትራክተሮቹ… Read more: ኮርፖሬሽኑ ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ ድረስ አገልግሎት የሚሰጡ ዎኪንግ ትራክተሮችን አስመጣ
- EABC earns 846 thousand USD from exporting incense & gumEthiopian Agricultural Businesses Corporation (EABC) has earned 846 thousand USD from exported incense, gum and myrrh in the concluded 2016 Ethiopian fiscal year. The foreign currency was obtained from offering 145 tons of forest products of incense, gum and myrrh. Moreover, an income of 13 million birr was obtained by providing 149.8 tons of forest products to the local market.EABC’s… Read more: EABC earns 846 thousand USD from exporting incense & gum
- ኮርፖሬሽኑ በስንዴ ልማት ለአበረከተው የላቀ አስተዋጽዖ እውቅና አገኘአዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በሀገር አቀፍ ደረጃ በስንዴ ልማት ከሀገራዊ ፍላጎት እስከ ውጭ ገበያ አቅራቢነት በመሸጋገር ሂደት ለአበረከተው የላቀ አስተዋጽዖ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቶታል።ኮርፖሬሽኑ ይህንን እውቅና ያገኘው “የመሻገር ጥሪቶች፣ የአዲስ ብርሃን ወረቶች” በሚል መሪ ሀሳብ ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም ‘የመሻገር ቀን’ በሳይንስ ሙዚየም በተከበረበት ወቅት ነው፡፡የኮርፖሬሽኑ የኦፕሬሽን ዐቢይ ዘርፍ ምክትል ዋና… Read more: ኮርፖሬሽኑ በስንዴ ልማት ለአበረከተው የላቀ አስተዋጽዖ እውቅና አገኘ
- ኮርፖሬሽኑ ከእጣን እና ሙጫ 846 ሺህ የአሜሪካን ዶላር አገኘአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2016 በጀት ዓመት 1 ሺህ 450 ኩንታል የእጣን፣ ሙጫ፣ ከርቤ እና አበከድ የደን ውጤቶችን ወደተለያዩ የዓለም ሀገራት በመላክ 846 ሺህ የአሜሪካ ዶላር አገኘ፡፡በተጨማሪም ለሀገር ውስጥ ገበያ 1 ሺህ 498 ኩንታል የእጣን፣ ሙጫ፣ ከርቤ እና አበከድ ምርቶችን በማቅረብ 13 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገቢ ማግኘት ችሏል፡፡በኮርፖሬሽኑ የአዳማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ… Read more: ኮርፖሬሽኑ ከእጣን እና ሙጫ 846 ሺህ የአሜሪካን ዶላር አገኘ
- ኮርፖሬሽኑ በአፈር ማዳበሪያ ግዥ፣ አቅርቦትና ሥርጭት መሳለጥ ለአበረከተው የጎላ አስተዋጽዖ ተሸለመአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2016/17 ምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ ግዥ፣ አቅርቦት እና ሥርጭት እንዲሳለጥ ለአበረከተው የጎላ አስተዋጽዖ ከግብርና ሚኒስቴር የእውቅና እና የምስጋና የምስክር ወረቀት እና ዋንጫ ተበረከተለት። በተመሳሳይ የኮርፖሬሽኑ የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ገብሬ መላክ የአፈር ማዳበሪያ የማጓጓዝ ሂደቱ እንዲሳለጥ እና ለተጠቃሚዎች በወቅቱ እንዲደርስ ለአበረከቱት የጎላ አስተዋጽዖ… Read more: ኮርፖሬሽኑ በአፈር ማዳበሪያ ግዥ፣ አቅርቦትና ሥርጭት መሳለጥ ለአበረከተው የጎላ አስተዋጽዖ ተሸለመ
- ለመስኖ እርሻ የሚውል የአፈር ማዳበሪያ የግዥ ሂደት ተጀመረለ2017/18 የምርት ዘመን 25 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ ይፈጸማልአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2017/18 የምርት ዘመን ለመስኖ እርሻ የሚውል ዳፕ እና ዩሪያ የአፈር ማዳበሪያ ከውጭ ለማጓጓዝ የግዥ ሂደት ጀመረ። በምርት ዘመኑ 25 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ ይፈጸማል።የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ ነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ.ም በሰጠው ውሳኔ መሰረት ለመስኖ እርሻ የሚውል ዳፕ እና… Read more: ለመስኖ እርሻ የሚውል የአፈር ማዳበሪያ የግዥ ሂደት ተጀመረ
- Ethiopian Investment Holdings’ CEO congratulates EABC staff on their successful achievements of 2016 fiscal yearAddis Ababa, September 3, 2024 (EABC): Ethiopian Investment Holdings’ (EIH) CEO Biruk Taye (PhD) congratulates Ethiopian Agricultural Businesses Corporation’s (EABC) management and staff on their successful achievements of 2016 Ethiopian fiscal year. The CEO has made comments during the EABC 2016 budget year employees final meeting and 2017 Ethiopian new year eve extraordinary entertainment program that was held on August… Read more: Ethiopian Investment Holdings’ CEO congratulates EABC staff on their successful achievements of 2016 fiscal year
- “ኮርፖሬሽኑ በ2016 በጀት ዓመት ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገቡ እንኳን ደስ ያላችሁ” የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ“ተቋሙ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዋልታ በመሆኑ ቦርዱ የሚጠበቅበትን ሁሉ ያደርጋል” የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባል አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2016 በጀት ዓመት ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገቡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) የተቋሙን የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።ዋና ሥራ አስፈጻሚው ይህን የገለጹት፣ የ2016 ዓ.ም የሠራተኞች ዓመታዊ የማጠቃለያ ስብሰባ… Read more: “ኮርፖሬሽኑ በ2016 በጀት ዓመት ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገቡ እንኳን ደስ ያላችሁ” የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ
- በ2016 እቅድ አፈጻጸም እና በ2017 እቅድ ዙሪያ ውይይት ተደረገአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች በ2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና በ2017 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ነሐሴ 21 ቀን 2016 ዓ.ም በኮርፖሬሽኑ ዋና መስሪያ ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተወያዩ።የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም የኮርፖሬሽኑ የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች ባደረጉት ሁለገብ ጥረት ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት ያቀዳቸውን ሥራዎች ማሳካት… Read more: በ2016 እቅድ አፈጻጸም እና በ2017 እቅድ ዙሪያ ውይይት ተደረገ
- የኮርፖሬሽኑ የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ጥሩ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ገለጸ* ቋሙ ተጨማሪ ገቢ የሚያስገኙ አዳዲስ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት ተጠቁሟል አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ጥሩ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (ኢኢሆ) ገለጸ።የኮርፖሬሽኑ አፈጻጸም ነሐሴ 17 ቀን 2016 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል በተገመገመበት ወቅት የውይይት መድረኩን የመሩት የኢኢሆ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር)፣ ኮርፖሬሽኑ በተጠናቀቀው… Read more: የኮርፖሬሽኑ የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ጥሩ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ገለጸ
- የኮርፖሬሽኑ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ሻራቸውን አኖሩአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):-የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በአንድ ጀንበር 600 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል የተላለፈውን ሀገራዊ ጥሪ ተከትለው ዛሬ ነሐሴ 17 ቀን 2016 ዓ.ም የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።በዕለቱ በተደረገ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ጠቀሜታ ያላቸው የጥላ ዛፍ ችግኞች በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት እና በቅርንጫፎች… Read more: የኮርፖሬሽኑ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ሻራቸውን አኖሩ
- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም የተቋሙ የማኔጅመንት አባላት እና የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ሥራ አስኪያጆች በተገኙበት እየተገመገመ ነው።ግምገማው በነገው ዕለትም የሚቀጥል ሲሆን፣ ነገ የኮርፖሬሽኑ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ይደረጋል። ### ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው! ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም
- ኮርፖሬሽኑ በአዲስ አበባ ያስገነባውን የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት አስመረቀ* በሌላ ዜና ለኮርፖሬሽኑ የውስጥ አገልግሎት የሚውሉ የዳቦ መጋገሪያ እና የጉድጓድ ውኃ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ያስገነባውን የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም አስመረቀ። ወይዘሮ አስናቀች ፀጋ ለተባሉ የወረዳ 6 ነዋሪ ከ1 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባውን መኖሪያ ቤት… Read more: ኮርፖሬሽኑ በአዲስ አበባ ያስገነባውን የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት አስመረቀ
- ኮርፖሬሽኑ የISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት የሙከራ ትግበራ ጀመረ* “የዛሬው ዕለት ለኮርፖሬሽኑ ታሪካዊ ቀን ነው” የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ * “የሀገሪቱ የምጣኔ ሀብት እድገት የጀርባ አጥንት ለሆነ ተቋም የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት እንዲተገብር የማማከር እና የመደገፍ ሥራ እያከናወንን በመሆኑ ታላቅ ደስታ እና ኩራት ይሰማናል” የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት የሙከራ… Read more: ኮርፖሬሽኑ የISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት የሙከራ ትግበራ ጀመረ
- ኮርፖሬሽኑ ሮቤ ከተማ ላይ ያስገነባው የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ተመረቀሮቤ፣ ሐምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በባሌ ሮቤ ከተማ 1 ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ ያስገነባው የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ሐምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተመርቆ የቁልፍ ርክክብ ተፈጽሟል። ኮርፖሬሽኑ መኖሪያ ቤቱን ያስገነባው በሮቤ ከተማ በሃቢፍቱ ቀበሌ ነዋሪ ለሆኑት ወይዘሮ መክዳ አብዱራሂም ነው። በምረቃ እና በቁልፍ ርክክብ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ… Read more: ኮርፖሬሽኑ ሮቤ ከተማ ላይ ያስገነባው የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ተመረቀ
- “ኮርፖሬሽኑ በግብርናው ዘርፍ የተሰጠውን ተልዕኮ እየተወጣና ትርፋማነቱን እያረጋገጠ በመዝለቁ ሊበረታታ ይገባል” በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ* የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ላይ ዘንድሮ የታየው አፈጻጸምም ጥሩ ነው ተብሏልአዲስ አበባ፣ ግንቦት 28/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በመንግሥት የተሰጠውን ተልዕኮ እየተወጣ እና ትርፋማነቱን እያረጋገጠ በመዝለቁ ሊበረታታ እንደሚገባ በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ይህ የተገለጸው የኮርፖሬሽኑ የ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር… Read more: “ኮርፖሬሽኑ በግብርናው ዘርፍ የተሰጠውን ተልዕኮ እየተወጣና ትርፋማነቱን እያረጋገጠ በመዝለቁ ሊበረታታ ይገባል” በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ
- Coming soonየግብርና ግብዓቶችን እና የእርሻ መሣሪያዎችን ከተቀጽላቸውና መለዋወጫቸው ጋር በማቅረብ እንዲሁም ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ የሚዘልቅ የተቀናጀ የግብርና ሜካናይዜሽን አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው የአርሶና አርብቶ አደሩ አለኝታ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ከቻይና የእርሻ መሣሪያዎች እና የኮንስትራክሽን ማምረቻ ኩባንያዎች በቅርቡ የሚያስመጣቸው ዶዘሮች፣ ስካቬተር፣ ዎኪንግ ትራክተሮች እና የሩዝ መሰብሰቢያ ማሽን (Rice combine harvester) ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!
- ኮርፖሬሽኑ በዘጠኝ ወራት ጥሩ አፈጻጸም ማስመዝገቡን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ አስታወቀአዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ጥሩ መሆኑን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ አስታወቀ።በግብርና ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ ሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም የተገመገመው የኮርፖሬሽኑ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በአራቱ የውጤት ተኮር እይታዎች ሲመዘን ጥሩ እንደሆነ የቦርድ ሰብሳቢው ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ተናግረዋል።ሰብሳቢው በቀጣዮቹ ሁለት ወራት ከኮርፖሬሽኑ የተሻለ ውጤት እንደሚጠበቅ ገልጸው፣ በእነዚህ… Read more: ኮርፖሬሽኑ በዘጠኝ ወራት ጥሩ አፈጻጸም ማስመዝገቡን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ አስታወቀ
- CEO of EABC held a discussion with a Chinese company* The company shows interest in working with EABC to supply Granular Urea and buy Natural GumAddis Ababa, May 24, 2024 (EABC): The Ethiopian Agricultural Businesses Corporation’s (EABC) Chief Executive Officer has discussed with Chinese high level delegation from China Petroleum Technology and Development Corporation (CPTDC).The Ethiopian Agricultural Businesses Corporation’s CEO, Kifle Woldemariam welcomed the officials of the company in… Read more: CEO of EABC held a discussion with a Chinese company
- ግብርናን ለማዘመን …ግብርናን ለማዘመን እየሰራ የሚገኘው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ከተቋቋመበት ከታህሳስ 2008 ዓ.ም ጀምሮ ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ የሚዘልቅ የተቀናጀ የሜካናይዜሽን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።ከዚህ በተጨማሪ ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ግብዓቶችን እንዲሁም የእርሻ መሣሪያዎችን ከእነተቀጽላቸው እና መለዋወጫቸው ጋር በተመጣጣኝ ዋጋ ለደንበኞቹ በማቅረብ ላይ ነው።በሌላ በኩል የእርሻ መሣሪያዎችን በከፊል በመገጣጠም፣ ዘር በማበጠር፣ የደረቅ ጭነት ትራንስፖርት በማመቻቸት እና ከሽያጭ በኋላ የቴክኒክና ሞያ፣ የምክርና የጥገና… Read more: ግብርናን ለማዘመን …
- 5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ ገብቷል – ዶክተር ግርማ አመንቴ(አዲስ አበባ፣ ጥር 10 ቀን 2016 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) የግብርና ሚኒስትሩ ዶ/ር ግርማ አመንቴ እና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትሩ ዶ/ር ዓለሙ ስሜ በ2016/17 ምርት ዘመን የአፈር ማደበሪያ አገባብ ዕቅድ ክንውን ላይ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በተያዘው የምርት ዘመን የግብርና ሚኒስቴር 23 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት አቅዶ ከክልሎች በተሰበሰበው የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎት መሰረት 19.4 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት 930 ሚሊዮን ዶላር… Read more: 5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ ገብቷል – ዶክተር ግርማ አመንቴ
- ኮርፖሬሽኑ 10 አጭዶመውቂያዎችንተረከበአዲስ አበባ፣ ህዳር 11/ 2016 ዓ.ም. (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከቻይና ያስመጣቸውን ‘ዙምላየን’ በመባል የሚታወቁ 10 አጭዶ መውቂያዎችን (combine harvesters) ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2016 ተረከበ፡፡ የአጭዶ መውቂያዎቹን ቁልፍ የዙምላየን ካምፓኒ ተወካይ ሚስተር አሊን ኪን ለኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም አስረክበዋል፡፡ በርክክቡ ወቅት አቶ ክፍሌ እንደተናገሩት፣ የቻይና የእርሻ እና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች አምራች ኩባንያ ከሆነው ዙምላየን ጋር ኮርፖሬሽኑ… Read more: ኮርፖሬሽኑ 10 አጭዶመውቂያዎችንተረከበ
- የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የምርት መሰብሰብ ሥራ አስጀመሩ ለበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የሚውል ዘር እየተሰበሰበ ነውአርዳይታ፣ ህዳር3/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአርዳይታ ቅድመ መስራች፣ መስራች እና የተመሰከረለት ዘር እርሻ ልማት የደረሰ ምርት የመሰብሰብ ሥራን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አስጀመሩ። ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ዛሬ ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም በአርዳይታ የዘር ማባዣ እርሻ ልማት ተገኝተው የምርት መሰብሰብ ሥራን አስጀምረዋል። የእርሻ ጣቢያው በ2015/16 የምርት ዘመን የስንዴ፣ ገብስ፣ ጎመን ዘር እና በቆሎ ሰብሎች… Read more: የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የምርት መሰብሰብ ሥራ አስጀመሩ ለበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የሚውል ዘር እየተሰበሰበ ነው
- “በአፈር ማዳበሪያ ግዥ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ለውጥ በመደረጉ ማዳበሪያ በመጠን፣ በጥራት፣ በተመጣጣኝ ዋጋ እና በጊዜ ለመግዛት እና ለማጓጓዝ ተችሏል” የግብርናሚኒስቴር “የማዳበሪያ ጉዳይ የሉዓላዊነት ጉዳይ በመሆኑ የእኛን አርበኝነት ይጠይቃል” የትራንስፖርትናሎ ጂስቲክስ ሚኒስቴርአዲስአበባ፣ጥቅምት 30/ 2016 ዓ.ም. (ኢግሥኮ)፡- በአፈር ማዳበሪያ ግዥ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ለውጥ በመደረጉ ማዳበሪያ በመጠን፣ በጥራት፣ በተመጣጣኝ ዋጋ እና በጊዜ ለመግዛት እና ለማጓጓዝ መቻሉን የግብርና ሚኒስትሩ ገለጹ። ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ይህን የገለጹት በአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ሥርጭት ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እና መፍትሔዎች ዙሪያ በአዳማ ኃይሌ ሪዞርት ሆቴል ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም በተደረገ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ነው፡፡በግብርና ሚኒስቴር… Read more: “በአፈር ማዳበሪያ ግዥ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ለውጥ በመደረጉ ማዳበሪያ በመጠን፣ በጥራት፣ በተመጣጣኝ ዋጋ እና በጊዜ ለመግዛት እና ለማጓጓዝ ተችሏል” የግብርናሚኒስቴር “የማዳበሪያ ጉዳይ የሉዓላዊነት ጉዳይ በመሆኑ የእኛን አርበኝነት ይጠይቃል” የትራንስፖርትናሎ ጂስቲክስ ሚኒስቴር
- የ2016/17 የሰብል ዘመን የአፈር ማዳበሪያ ግዥና ሥርጭትን በተመለከተ:- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ክፍሌ ወልደማርያም እና በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ኢንቨስትመንት እና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ለኢቲቪ የሰጡት መግለጫ
- ኮርፖሬሽኑ ከውጭ ያስመጣቸውን ትራክተሮች ለፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሽያጭ አስረከበአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአውሮፓ ካስመጣቸው ‘ዜቶር’ ትራክተሮች ውስጥ ስምንት ትራክተሮችን ከእነተቀጽላቸው ‘ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ’ በመባል ለሚታወቅ ድርጅት በሽያጭ አስረከበ፡፡ ድርጅቱ ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ስምንት ትራክተሮችን፣ ስምንት ማረሻዎችን፣ ሦስት መከስከሻዎችን እና ሦስት መስመር ማውጫዎችን ከኮርፖሬሽኑ ገዝቷል። ዛሬ ጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም በኮርፖሬሽኑ ዋና መስሪያ ቤት በተካሄደ የርክክብ ሥነ ሥርዓት ላይ… Read more: ኮርፖሬሽኑ ከውጭ ያስመጣቸውን ትራክተሮች ለፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሽያጭ አስረከበ
- ኮርፖሬሽኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኮንትራት እርሻ እያባዛ የሚገኘውን የድቃይ በቆሎ የተመሰከረለት የዘር ማሳ አስጎበኘኮርፖሬሽኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኮንትራት እርሻ እያባዛ የሚገኘውን የድቃይ በቆሎ የተመሰከረለት የዘር ማሳ አስጎበኘ * የክልሉ መንግሥት ኮርፖሬሽኑ ላቀረበው ተጨማሪ የዘር ማባዣ መሬት ጥያቄ ምላሽ እንደሚሰጥ አስታውቋል ============================ አሶሳ፣ ጥቅምት 27/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኮንትራት እርሻ ከባለሀብት ጋር እያባዛ የሚገኘውን የድቃይ በቆሎ የተመሰከረለት የዘር ማሳ ለክልል፣ ዞን፣ ወረዳ እና ቀበሌ አመራሮች ጥቅምት 27 ቀን… Read more: ኮርፖሬሽኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኮንትራት እርሻ እያባዛ የሚገኘውን የድቃይ በቆሎ የተመሰከረለት የዘር ማሳ አስጎበኘ
- ኮርፖሬሽኑ ከአውሮፓ ከሚያስመጣቸው 75 ትራክተሮች ውስጥ 59ኙን ተረከበአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22/2016 ዓ.ም. (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአውሮፓ ከሚያስመጣቸው 75 ትራክተሮች ውስጥ 59ኙን ተረከበ። በኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎች አቅርቦት፣ ማርኬቲንግና ሽያጭ መምሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ቶሎሳ እንዳስታወቁት፣ ኮርፖሬሽኑ የሀገሪቷን ግብርና ለማዘመን የሚያስችሉ የእርሻ መሣሪያዎችን ከእነተቀጽላቸው ከአውሮፓ እና ከቻይና እያስመጣ ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ ኮርፖሬሽኑ ከ110 እስከ136 የፈረስ ጉልበት ያላቸውን ‘ዜቶር’ በመባል የሚታወቁ ትራክተሮችን ከቼክ ሪፐብሊክ… Read more: ኮርፖሬሽኑ ከአውሮፓ ከሚያስመጣቸው 75 ትራክተሮች ውስጥ 59ኙን ተረከበ
- ኮርፖሬሽኑ የአርሶ አደሮች እና የባለሀብቶች ሰብል እየሰበሰበ ነውለመተሃራ ስኳር ፋብሪካ 700 ሄክታር የሸንኮራ አገዳ ማሳ እያዘጋጀ ይገኛልአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23/2016 ዓ.ም. (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአርሶ አደሮችን፣ በግብርና ሥራ የተሰማሩ ባለሀብቶችን እና የተለያዩ ድርጅቶችን የደረሰ ሰብል በተመጣጣኝ ዋጋ እየሰበሰበ ነው፡፡በኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎች እና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ ክፍሌ እንደገለጹት፣ ኮርፖሬሽኑ ከጥቅምት 2016 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ በሞጆ እና ሄረሮ ዙሪያ ለሚገኙ አርሶ አደሮች እና… Read more: ኮርፖሬሽኑ የአርሶ አደሮች እና የባለሀብቶች ሰብል እየሰበሰበ ነው
- ኮርፖሬሽኑ በትራክተር የሚጎተቱ ጣልያን ሰራሽ የኬሚካል መርጫ ማሽኖችን አስመጣከቻይናው ዙምላይን የገዛቸው ኮምባይን ሀርቨስተሮችም ጂቡቲ ወደብ ደርሰዋልአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 19/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):-የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) በትራክተር የሚጎተቱ 15 ጣልያን ሰራሽ የኬሚካል መርጫ ማሽኖችን በ425 ሺህ 280 የአሜሪካን ዶላር (23 ሚሊዮን 605 ሺህ 251.456 ብር) አስመጣ።በእርሻ መሣሪያዎች እና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ የእርሻ መሣሪያዎች አቅርቦት፣ ማርኬቲንግና ሽያጭ መምሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ቶሎሳ እንዳስታወቁት፣ እያንዳንዱ ማሽን 3 ሺህ ሊትር አግሮኬሚካሎችን… Read more: ኮርፖሬሽኑ በትራክተር የሚጎተቱ ጣልያን ሰራሽ የኬሚካል መርጫ ማሽኖችን አስመጣ
- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአቢሲኒያ የጥራት ሽልማት ድርጅት የተዘጋጀውን የመጀመሪያ የኢንደስትሪ ሽልማት አገኘ።በኢንተርሌግዠሪ ሆቴል መጋቢት 24/2015 ዓ.ም. በተዘጋጀ የኢንደስትሪ ሽልማት መርሐ ግብር ላይ ኮርፖሬሽኑ የወርቅ ዋንጫ፣ የወርቅ ሜዳሊያ እና ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ አግኝቷል። ሽልማቱን ከዕለቱ የክብር እንግዳ የኢፌዴሪ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) እጅ የተቀበሉት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ናቸው። በተመሳሳይ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም በግላቸው የሥራ አመራር ከፍተኛ የክብር ኮርደን/GOLD Honor CORD ሽልማት እና በኢንደስትሪ… Read more: የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአቢሲኒያ የጥራት ሽልማት ድርጅት የተዘጋጀውን የመጀመሪያ የኢንደስትሪ ሽልማት አገኘ።
- በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የኮፈሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከ117 ሺህ ኩንታል በላይ ዘር መሰብሰቡን አስታወቀየቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ቡሹራ መሐመድ እንዳስታወቁት፣ ጽ/ቤቱ በ2014/15 የምርት ዘመን በባሌ እና አርሲ ዞኖች ከባለሀብቶች እና የግብርና ኮሌጆች በኮንትራት ማዕቀፍ 120 ሺህ ኩንታል ዘር ለማምረት አቅዶ፣ ከ117 ሺህ ኩንታል በላይ ማግኘት ተችሏል ብለዋል፡፡ ይህም የእቅዱን 97.5 ከመቶ ነው ያሉት አቶ ቡሹራ፣ የተሰበሰበው ምርት በጽ/ቤቱ ታሪክ ከፍተኛው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ከተሰበሰበው ዘር ውስጥም ከ10 በላይ የስንዴ እና ገብስ ዝርያዎች መሆናቸውን… Read more: በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የኮፈሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከ117 ሺህ ኩንታል በላይ ዘር መሰብሰቡን አስታወቀ
- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በመንግሥት ከተሰጠው ሰፊ ተልዕኮ አንጻር የበርካታ ቋሚ ኮሚቴዎች ድጋፍ እንደሚያስፈልገው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ገለጹ፡፡የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ፕሮፌሰር ዶክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዶ ይህንን የገለጹት፣ ኮርፖሬሽኑ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአዳማና በአዲስ አበባ ከተሞች ከመጋቢት 8-9/2015 ዓ.ም. ድረስ ባዘጋጀው የውይይትና የጉብኝት መርሐ ግብር ማጠቃለያ ነው፡፡ ኮርፖሬሽኑ ግብርናን ለማዘመን እያከናወናቸው ለሚገኘው ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ቋሚ ኮሚቴው በቀጣይ ከሚያደርገው ድጋፍ ባሻገር የኮርፖሬሽኑ ሥራዎች የሚመለከታቸው ሌሎች ቋሚ ኮሚቴዎች ተቋሙን ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው ፕሮፌሰር… Read more: የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በመንግሥት ከተሰጠው ሰፊ ተልዕኮ አንጻር የበርካታ ቋሚ ኮሚቴዎች ድጋፍ እንደሚያስፈልገው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ገለጹ፡፡
- በኮርፖሬሽኑ የባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከ859 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን የግብርና ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን ማሰራጨቱን ገለጸአዲስ አበባ፣ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከ859 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን የግብርና ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን ለተጠቃሚዎች ማሰራጨቱን አስታወቀ፡፡ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የ2015 በጀት ዓመት የሰባት ወራት የሥራ አፈጻጸሙን አስመልክቶ ለኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን የሥራ ክፍል በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ የቅባት እህሎችን ዘር ወደ ውጭ ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሬን ለማስገኘት እየተንቀሳቀሰ ሲሆን፣ በተለይም አኩሪ አተር… Read more: በኮርፖሬሽኑ የባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከ859 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን የግብርና ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን ማሰራጨቱን ገለጸ
- ኮርፖሬሽኑ በዘንድሮ የመኸር ምርት ዘመን እስካሁን 195 ሺህ ኩንታል የተሻሻለ የምርጥ ዘር መሰብሰቡን ገለጸአዲስ አበባ (ኢዜአ) ጥር 20 ቀን 2015፡- በ2014/15 የመኸር ምርት ዘመን እስካሁን 195 ሺህ ኩንታል የተሻሻለ ምርጥ ዘር መሰብሰቡን የኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ገለጸ። ኮርፖሬሽኑ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ በ2014/15 የመኸር የምርት ዘመን ምርት ለመሰብሰብ በያዘው ዕቅድ መሰረት የመሰብሰብ ሥራውን እያከናወነ መሆኑን አስታውቋል። በምርት ዘመኑ 338 ሺህ ኩንታል ለመሰብሰብ ዕቅድ መያዙን ጠቅሶ፣ እስካሁን 195 ሺህ ኩንታል በመሰብሰብ እያጓጓዘ መሆኑን ገልጿል።… Read more: ኮርፖሬሽኑ በዘንድሮ የመኸር ምርት ዘመን እስካሁን 195 ሺህ ኩንታል የተሻሻለ የምርጥ ዘር መሰብሰቡን ገለጸ
- ለ2015/16 የሰብል ዘመን 573 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች የመጀመሪያዋ መርከብ ጅቡቲ ወደብ ደረሰችየኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ለ2015/16 የሰብል ዘመን ከሞሮኮው የአፈር ማዳበሪያ አምራች ኦ ሲ ፒ ኩባንያ ከገዛው 7 ሚሊዮን 875 ሺህ 520 ኩንታል ማዳበሪያ (NPS family) ውስጥ የመጀመሪያው 572 ሺህ 950 ኩንታል NPS የአፈር ማዳበሪያ ጂቡቲ ወደብ ደረሰ። ዛሬ ታህሳስ 18/2015 ዓ.ም. ከቀኑ 8:00 ላይ ወደብ የደረሰው ማዳበሪያ MV Great Comfort በተባለች የመጀመሪያዋ መርከብ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከሰባት ቀን… Read more: ለ2015/16 የሰብል ዘመን 573 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች የመጀመሪያዋ መርከብ ጅቡቲ ወደብ ደረሰች
- ኮርፖሬሽኑ ከአውሮፓ ከሚያስመጣቸው 115 ትራክተሮች ውስጥ የመጀመሪያዎቹ 30 ትራክተሮች በቅርቡ አዲስ አበባ ይገባሉየኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) በዚህ ዓመት ከአውሮፓ ከሚያስመጣቸው 115 ትራክተሮች ውስጥ የመጀመሪያዎቹን 30 ትራክተሮች ከአንድ ወር በኋላ ይረከባል፡፡ በኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎችና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ ክፍሌ እንደተናገሩት፣ ኮርፖሬሽኑ 11.7 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ግምት ያላቸውን የተለያዩ የእርሻ መሣሪያዎች፣ ተቀጽላዎች/Implements እና መለዋወጫዎች ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኤልሲ ከተከፈተላቸው የእርሻ መሣሪያዎች ውስጥ የቼክ ሪፐብሊክ ስሪት… Read more: ኮርፖሬሽኑ ከአውሮፓ ከሚያስመጣቸው 115 ትራክተሮች ውስጥ የመጀመሪያዎቹ 30 ትራክተሮች በቅርቡ አዲስ አበባ ይገባሉ
- ኮርፖሬሽኑ ከ103 ሺህ ኩንታል በላይ የአርሶ አደሮችን እና የሌሎች ምርጥ ዘር አባዥዎችን ምርት በመሰብሰብ አስረከበአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 14/2015 ዓ.ም (ኢግሥኮ) ፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) የአርሶ አደሮች፣ የባለሃብቶች እና የመንግሥት ተቋማት ምርጥ ዘር አባዥዎችን የደረሱ ሰብሎች በተመጣጣኝ ዋጋ በመሰብሰብ አስረከበ፡፡ በኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎችና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ ክፍሌ እንደተናገሩት፣ ኮርፖሬሽኑ እስከ ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ 90 ሺህ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ አቅዶ ከ103 ሺህ ኩንታል በላይ የደረሰ ሰብል በመሰብሰብ… Read more: ኮርፖሬሽኑ ከ103 ሺህ ኩንታል በላይ የአርሶ አደሮችን እና የሌሎች ምርጥ ዘር አባዥዎችን ምርት በመሰብሰብ አስረከበ
- ኮርፖሬሽኑን ከፍተኛ ደረጃ ላይ ለማድረስ በበጀት ዓመቱ የተያዘውን እቅድ ማሳካት ይጠበቅብናል” የኢግሥኮ ዋና ሥራ አስፈጻሚየኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) በ2015 በጀት ዓመት ለመፈጸም ያቀዳቸው ሥራዎች እንዲሳኩ የጋራ ጥረት እንዲደረግ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ይህን ማሳሰቢያ የሰጡት፣ ከጥር 1 ቀን ጀምሮ ሥራ ላይ በሚውል የተከለሰ እቅድ ዙሪያ ከኮርፖሬሽኑ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ የስብሰባ አዳራሽ ዛሬ ታህሳስ 11 ቀን 2015 ዓ.ም. በተደረገ ውይይት ነው፡፡… Read more: ኮርፖሬሽኑን ከፍተኛ ደረጃ ላይ ለማድረስ በበጀት ዓመቱ የተያዘውን እቅድ ማሳካት ይጠበቅብናል” የኢግሥኮ ዋና ሥራ አስፈጻሚ
- Agri Business Magazine 2022 G.C_2015_EC
- የኮርፖሬሽኑ የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሦስት ክልሎች በኮንትራት እርሻዎች ምርጥ ዘር እያባዛ ነውአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሦስት ክልሎች በኮንትራት እርሻዎች የተለያዩ ሰብሎች ምርጥ ዘር እያባዛ ይገኛል፡፡ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ አድማሱ አናጋው እንዳስታወቁት፣ ጽ/ቤቱ በተያዘው የ2014/15 የመኸር ወቅት በኮንትራት አባዥ ሰፋፊ የባለሃብት እርሻዎች፣ በመንግሥት የግብርና ተቋማት እና በአርሶ አደር ማሳዎች ላይ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ እና ምስራቅ ሸዋ ዞኖች፣ በደቡብ… Read more: የኮርፖሬሽኑ የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሦስት ክልሎች በኮንትራት እርሻዎች ምርጥ ዘር እያባዛ ነው
- በኮርፖሬሽኑ የጎንዴ ኢተያ መስራች ዘር ማባዣ እርሻ ልማት እና በኮንትራት እርሻዎች ከ111 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃልአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11/2015 ዓ.ም (ኢግሥኮ) በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአሰላ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አማካኝነት በጎንዴ ኢተያ መስራች ዘር ማባዣ እርሻ ልማት እንዲሁም በሰፋፊ የባለሃብትና የአርሶ አደር የኮንትራት እርሻዎች በዘር ከተሸፈነው 3 ሺህ 15 ሄክታር መሬት ከ111 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተገለጸ፡፡ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ብርሃኑ የሺጥላ እንደገለጹት፣ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የራሱ እርሻዎች በሆኑት የጎንዴ ኢተያ እንዲሁም በሰፋፊ የባለሃብት… Read more: በኮርፖሬሽኑ የጎንዴ ኢተያ መስራች ዘር ማባዣ እርሻ ልማት እና በኮንትራት እርሻዎች ከ111 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል
- ኮርፖሬሽኑ ከአርዳይታ እርሻ ልማት ከ85 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ይጠብቃልአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15/2015 ዓ.ም. (ኢግሥኮ):- በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስር ከሚተዳደሩት እርሻዎች አንዱ በሆነው የአርዳይታ ምርጥ ዘር ማባዣ እርሻ ልማት ከ85 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገለጸ፡፡ የአርዳይታ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍቃዱ ከበደ እንደገለጹት፣ በ2014/15 የመኸር ወቅት 3 ሺህ 70 ሄክታር መሬት በቅድመ መስራች፣መስራች እና የተመሰከረለት ዘር ደረጃዎች መሸፈን ተችሏል፡፡ ከዚህ ውስጥ 2 ሺህ… Read more: ኮርፖሬሽኑ ከአርዳይታ እርሻ ልማት ከ85 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ይጠብቃል
- ኮርፖሬሽኑ የምርጥ ዘር አቅርቦትን ለማሳደግ ከባለሃብቶች ጋር እየሰራ ነውአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለተጠቃሚዎች የሚያቀርበውን ምርጥ ዘር በጥራትና በመጠን ለማሳደግ በኮንትራት ሰፋፊ እርሻዎች ከባለሃብቶች ጋር እየሰራ ነው። የይስሃቅ ሳምሶን እርሻ ልማት እና የዱቄት ፋብሪካ ባለቤት አቶ ይስሃቅ ሳምሶን ከኮርፖሬሽኑ ጋር ምርጥ ዘር ማባዛት ከጀመሩ ሶስት ዓመት እንደሆናቸው ገልጸው፣ በዚህ ዓመት ከኮርፖሬሽኑ ኮፈሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር ውል በመግባት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ባሌ… Read more: ኮርፖሬሽኑ የምርጥ ዘር አቅርቦትን ለማሳደግ ከባለሃብቶች ጋር እየሰራ ነው
- ኮርፖሬሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ62 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን የግብርና ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን ለተጠቃሚዎች አቅርቧልየኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2014 በጀት ዓመት ከ62 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን የግብርና ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን ለተጠቃሚዎች አቅርቧል፡፡ በኮርፖሬሽኑ የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ገብሬ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ኮርፖሬሽኑ ምርትና ምርታማነትን የሚጨምሩ የአፈር ማዳበሪያ፣ የሰብል ተባይ ማጥፊያ አግሮኬሚካሎች እና ኬሚካል መርጫ መሣሪያዎችን ከዓለም አቀፍ አቅራቢዎች በመግዛት ለተጠቃሚዎች ማቅረብ ችሏል፡፡ በዚህ መሰረት ለ2014/15 የሰብል ዘመን… Read more: ኮርፖሬሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ62 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን የግብርና ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን ለተጠቃሚዎች አቅርቧል
- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2014/15 የምርት ዘመን 14 ሺህ 141 ሄክታር መሬት በዘር በመሸፈን 361 ሺህ 156 ኩንታል ምርጥ ዘር ለማባዛት አቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷልኮርፖሬሽኑ በሀገር ደረጃ ከ30 በመቶ በላይ የሚሆነውን የምርጥ ዘር ፍላጎት እያቀረበ እንደሚገኝ የገለጹት በኮርፖሬሽኑ የኢትዮጵያ የምርጥ ዘር አቅርቦት እና የደን ውጤቶች አቅርቦት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዘነበ ወልደሥላሴ፣ በምርት ዘመኑ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችሉ ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅት ኮርፖሬሽኑ 68 በመቶ የሚሆነውን ምርጥ ዘር በሰፋፊ የመንግሥት እና ባለሀብት እርሻዎች እና በአርሶ አደር ማሳ፣ ቀሪውን 32 በመቶ ደግሞ… Read more: የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2014/15 የምርት ዘመን 14 ሺህ 141 ሄክታር መሬት በዘር በመሸፈን 361 ሺህ 156 ኩንታል ምርጥ ዘር ለማባዛት አቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል
- ኮርፖሬሽኑ 181 ትራክተሮችን ከነመለዋወጫቸው እና ተቀጥላቸው ሊያቀርብ ነው* በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 46 የአውሮፓ ስሪት ትራክተሮችን ለተጠቃሚዎች አቅርቧል የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2015 በጀት ዓመት 181 ትራክተሮችን ከነመለዋወጫቸው እና ተቀጥላቸው ከውጭ ገበያ በማስመጣት ለተጠቃሚዎች ሊያቀርብ ነው፡፡ በኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎች እና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግስቱ ክፍሌ እንደገለጹት፣ ለአማራ ክልል 75 እንዲሁም ለአርሶ አደሮች እና በሰፋፊ እርሻ ለተሰማሩ ባለሃብቶች 106 በድምሩ 181 ዘመናዊ እና አስተማማኝ… Read more: ኮርፖሬሽኑ 181 ትራክተሮችን ከነመለዋወጫቸው እና ተቀጥላቸው ሊያቀርብ ነው
- ኮርፖሬሽኑ 46 ትራክተሮችን ለተጠቃሚዎች አስረከበየኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ከ151 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 46 ዱዝ-ፋር (DEUTZ-FAHR) ትራክተሮችንከጣሊያንሀገርበማስመጣትለተጠቃሚዎችበሽያጭ አስረክቧል፡፡ ከ110 እስከ 180 የፈረስ ጉልበት ያላቸው እነዚህ ትራክተሮች በሽያጭ የቀረቡት ለአማራ ክልል ግብርና ቢሮ፣ ለሲዳማ ክልል እርሻ እና የተፈጥሮ ሃብት ቢሮ እንዲሁም ለእንጅባራ፣ ደብረ ብርሃን እና ጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች፤ ለአጋርፋ ግብርና ኮሌጅ እና በእርሻ ሥራ ላይ ለተሰማሩ ባለሃብቶች ነው፡፡ ትራክተሮቹ የ2021 እና 2022 ምርት በመሆናቸው… Read more: ኮርፖሬሽኑ 46 ትራክተሮችን ለተጠቃሚዎች አስረከበ
- “ለኮርፖሬሽኑ ምርጥ ዘር ለሚያባዙ ባለሃብቶች የምናደርገውን ድጋፍ አጠናክረን እንቀጥላለን” የኢግሥኮ ዋና ሥራ አስፈጻሚከኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ጋር ውል ገብተው ምርጥ ዘር እያባዙ ለሚገኙ ባለሃብቶች ኮርፖሬሽኑ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ይህን የገለጹት፣ በምስራቅ ባሌ ዞን በኮንትራት እርሻ ለኮርፖሬሽኑ የምርጥ ዘር እያባዙ ከሚገኙ ባለሃብቶችና የባለድርሻ አካላት ጋር በቢሾፍቱ ያቱ ሆቴል ግንቦት 28/2014 ዓ.ም. በተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ ነው፡፡ “እናንተ ዘር የምታባዙት ለእኛ… Read more: “ለኮርፖሬሽኑ ምርጥ ዘር ለሚያባዙ ባለሃብቶች የምናደርገውን ድጋፍ አጠናክረን እንቀጥላለን” የኢግሥኮ ዋና ሥራ አስፈጻሚ
- የደን ውጤት ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ ከ900 ሺህ ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷልነሐሴ 4/2013 (ኢዜአ) የደን ውጤት የሆኑ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ ከ900 ሺህ ዶላር በላይ መገኘቱን የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ገለፀ። የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም የተቋሙን የ2013 በጀት ዓመት ስራ አፈፃፀም አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው የምርጥ ዘር፣ የደን ውጤቶችና የግብርና ምርት ማሳደጊያ አቅርቦቶችን ጨምሮ የእርሻ መሳሪያዎች አቅርቦትና የሜካናይዜሽን አገልግሎትን ከማስፋት አኳያ የተሰሩ ስራዎችን አብራርተዋል። የደን ውጤቶች የሆኑትን እንደ… Read more: የደን ውጤት ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ ከ900 ሺህ ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል
- የግብርና ሚኒስትሩና የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ የአሰላ ቅርንጫፍ ጎንዴ ኢተያ እርሻ ጣቢያዎችን ጎበኙየግብርና ሚኒስትሩና የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ አመራር ቦርድ የአሰላ ቅርንጫፍ ጎንዴ ኢተያ እርሻ ጣቢያዎችን ነሐሴ 16/2013 ዓ.ም ጎበኙ። በጉብኝቱ ወቅት የተገኙት የኢፌዲሪ የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ ዑመር ሁሴን፣ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ግርማ አመንቴ እና የኮርፖሬሽኑ የቦርድ አባላት አሰላ ቅርንጫፍ ጎንዴ ኢተያ እርሻ ጣቢያዎች ላይ የተዘሩ የጤፍ፣ ስንዴ፣ ባቄላ፣ ጎመን፣ ተልባ፣ ሽምብራና በቆሎ የሰብል… Read more: የግብርና ሚኒስትሩና የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ የአሰላ ቅርንጫፍ ጎንዴ ኢተያ እርሻ ጣቢያዎችን ጎበኙ
- ኮርፖሬሽኑን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ አዳዲስ ሃሳቦችን ማፍለቅ እንደሚገባ ተገለጸ“ኮርፖሬሽኑ ካለው አፈጻጸምና ልምድ አንጻር በ2014 በጀት ዓመት የተሻለ ውጤት እንደሚያስመዘግብ ተስፋ አደርጋለሁ” የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽንን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ አዳዲስ ሃሳቦችን ማፍለቅ እንደሚገባ የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ገለጹ፡፡ የቦርድ ሰብሳቢው ዶክተር ግርማ አመንቴ ይህንን የገለጹት ነሐሴ 22/2013 ዓ.ም በተካሄደ የኮርፖሬሽኑ የሠራተኞች አመታዊ ስብሰባ ላይ ነው፡፡ በስብሰባው ወቅት የተቋሙ የ2013 በጀት ዓመት አፈጻጸምና… Read more: ኮርፖሬሽኑን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ አዳዲስ ሃሳቦችን ማፍለቅ እንደሚገባ ተገለጸ






















































































