የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

ኮርፖሬሽኑ 181 ትራክተሮችን ከነመለዋወጫቸው እና ተቀጥላቸው ሊያቀርብ ነው

   

አቶ መንግስቱ ክፍሌ
የእርሻ መሣሪያዎች አቅርቦትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ

        * በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 46 የአውሮፓ ስሪት ትራክተሮችን ለተጠቃሚዎች አቅርቧል

የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2015 በጀት ዓመት 181 ትራክተሮችን ከነመለዋወጫቸው እና ተቀጥላቸው ከውጭ ገበያ በማስመጣት ለተጠቃሚዎች ሊያቀርብ ነው፡፡

በኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎች እና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግስቱ ክፍሌ እንደገለጹት፣ ለአማራ ክልል 75 እንዲሁም ለአርሶ አደሮች እና በሰፋፊ እርሻ ለተሰማሩ ባለሃብቶች 106 በድምሩ 181 ዘመናዊ እና አስተማማኝ ትራክተሮችን ለማቅረብ ዝግጅት ተጀምሯል፡፡

የእርሻ መሣሪያዎች የግብርናን ሥራ በማዘመን ምርትና ምርትማነትን በከፍተኛ ደረጃ ይጨምራሉ ያሉት አቶ መንግስቱ፣ ኮርፖሬሽኑ በ2014 በጀት ዓመት በ179 ሚሊዮን ብር ወጪ ከ110 እስከ 180 የፈረስ ጉልበት ያላቸው 46 ትራክተሮችን ከነተቀጥላቸው ከጣሊያን ሀገር በማስመጣት ለተጠቃሚዎች ማቅረቡንም ተናግረዋል፡፡

በአጠቃላይ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ221 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የእርሻ መሣሪያዎች፣ ተቀጥላዎች (ማረሻ፣ መከስከሻ፣ መስመር ማውጫ፣ ዘር መዝሪያ) እና የትራክተር ጋሪዎች ለተጠቃሚዎች መቅረባቸውን ነው ሥራ አስፈጻሚው የገለጹት፡፡

በተጨማሪም 108 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ዋጋ ያላቸው የእርሻ መሣሪያዎች፣ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች እና የከባድ ተሽከርካሪዎች ጎማ፣ ባትሪ፣ ፊልተር እና ሌሎች መለዋወጫዎችንም አቅርበናል ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል በግብርና ሜካናይዜሽን አገልግሎት የመሬት እና የማሳ ዝግጅት እንዲሁም የምርት መሰብሰብ ሥራዎች ለተጠቃሚዎች ተደራሽ መደረጋቸውን አቶ መንግስቱ አስታውቀዋል፡፡

ከምርት መሰብሰብና ማጓጓዝ አኳያም ሲገልጹ፣ “በዋናነት ለአርሶ አደሮች 192 ሺህ ኩንታል ምርት አጭደን፣ ወቅተን እና አጓጉዘን እስከ ማከማቻ በማድረስ የምርት ብክነት እንዲቀንስ፣ የአርሶ አደሩ ምርታማነት እንዲጨምር እንዲሁም ጊዜውና ጉልበቱ እንዲቆጠብ አድርገናል” ብለዋል፡፡    

በመሬት ዝግጅት ረገድም በኦሞ ኩራዝና ጣና በለስ የስኳር ልማት ፕሮጀክቶች ለሸንኮራ አገዳ ልማት እና ለኮርፖሬሽኑ የምርጥ ዘር ማባዣ የሚውል 1 ሺህ 200 ሄክታር መሬት ለእርሻ ምቹ ተደርጎ በኮርፖሬሽኑ መዘጋጀቱንም ተናግረዋል፡፡

በማሣ ዝግጅትም 5 ሺህ 862 ሄክታር መሬት በማረስ፣ በመከስከስ እና ዘር በመዝራት ለተጠቃሚዎች አገልግሎት መሰጠቱን ገልጸዋል፡፡

በ2015 በጀት ዓመት በ15 የምርት መሰብሰቢያ ኮምባይነሮች እና በ10 የደረቅ ጭነት ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎች በመታገዝ የተሻለ የሜካናይዜሽን አገልግሎት ለመስጠት በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ የተናገሩት አቶ መንግስቱ፣ ስለ ትራክተር አያያዝ እና አጠቃቀም በስፋት ሥልጠና ለመስጠት መዘጋጀታቸውንም አያይዘው ጠቁመዋል፡፡

                                                                      ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!

የኢግሥኮ አመሠራረት

የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) በግብርናው ዘርፍ ከ30 እስከ 38 ዓመት ልምድ ያካበቱ አምስት ነባር ድርጅቶችን ማለትም የኢትዮጵያ ምርጥ ዘር ድርጅት፣ የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅራቢ ድርጅት፣ የእርሻ መሳሪያዎችና የቴክኒክ አገልግሎት አክሲዮን ማህበር፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ድርጅት እና የተፈጥሮ ሙጫ ምርትና ገበያ ልማት ድርጅቶችን በማዋሃድ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 368/2008 መሠረት ታህሳስ 2008 ዓ.ም የተቋቋመ መንግሥታዊ የልማት ድርጅት ነው፡፡

ይህን መረጃ ለማግኘት እዚህ ይጫኑ (Please click here to download the profile document)

Establishment

Establishment

The Ethiopian Agricultural Businesses Corporation (EABC) is established as a federal government public enterprise by Council of Ministers Regulation Number 368/2015 with the authorized capital of birr 2 billion 440 million of which birr 610 million is paid up in cash and in kind.

The corporation was formed by merging five state owned Enterprises; namely Ethiopian Seed Enterprise, Agricultural Inputs Supply Enterprise, Agricultural Equipment and Technical Services Share Company, Agricultural Mechanization Service Enterprise, and Natural Gum Processing and Marketing Enterprises.

Currently, the corporation which has 24 branches and stations in different regions, is accountable to Public Enterprises Holding Administration and managed by board of directors.

For achieving the mission, the corporation is supplying agricultural inputs (improved seeds, fertilizers & agrochemicals), reliable, modern and high quality agricultural machineries and spare parts, construction equipment and chemical spraying equipment at affordable price.

Besides, importing and assembling agricultural equipment, rendering integrated agricultural mechanization and maintenance service as well as providing rental services of agricultural machineries and transport vehicles (heavy goods vehicles), consultancy and technical training services are among the duties and responsibilities of the corporation.

Since its establishment in December 2015 EABC has registered a remarkable achievement in the sector. In line with this promising result, the corporation has also endeavored to continue to play an important role in modernizing agriculture, boosting production and productivity at the national level.

As a result, the corporation has been able to meet its authorized capital in five years period and this can be taken as one of an indication of its success over the previous years. Overall, the corporation is contributing to the modernization of agriculture and the growth of productivity through integrated agricultural development activities from land preparation to warehouse.

Purposes of Establishment

The purpose for which the Corporation is established are:

1. to buy from domestic and international markets and supply agricultural inputs, process same; undertake agricultural inputs market price stabilization activities;

2. to render agricultural mechanization services, agricultural and construction equipment repair services and provide rental services of agricultural machineries and transport vehicles;

3. to buy from domestic and international markets and supply agricultural machineries and spare parts, construction equipment and agro-chemicals;

4. to provide necessary education for promotion of the use of modern agricultural machineries; provide consultancy service in handling and use of agricultural machineries and provide on the job technical trainings;

5. to harvest, buy, value add to and process natural gum, produce other forest products, and supply to domestic and international markets;

6. to undertake agricultural land development studies and preparation of designs, agricultural land surveying, clearing,  leveling, drainage end irrigation activities as well as other activities  related to agricultural land development;

7. to cause undertaking of feasibility studies, design preparation, technology selection and negotiation, erection and commissioning of new and expansion projects as well as for research activities;

8. to cause the local designing and manufacturing of agricultural machineries and spare parts in partnership with capable local and foreign companies;

9. to work in cooperation with the concerned educational research and training institutions in producing trained manpower in such fields, numbers and quality as required by the sector,

10.  to undertake studies, based on direction given to it by the Ministry of Public Enterprises, for the acquisition of financial, technological and modem governance inputs (including attracting investments or participating in investments) that can help it to become competitive; both locally and globally, and profitable and implement same upon approval;

11. to multiply, clean and process pre-basic, basic and certified seeds of various crop; vegetables and fruits; where necessary import pre-basic seeds and cause their production or sale them; to sell byproducts;

12. to undertake research and implement improvements with respect to the supply of agricultural inputs, agricultural machineries repair, the production and marketing of natural gum, mechanization services and related matters and thereby ensure its competitiveness.

13. to sell bonds, collateralize, negotiate and sign loan agreements with local and foreign sources in accordance with directives issued by the Ministry of Finance and Economic Corporation and on the basis of the guidance of Ministry of Public Enterprise;

14. to engage in other related activities for the attainment of its purposes.

Organizational Set-up Currently, EABC is organized into two sectors namely Corporate Operation main Sector and Corporate Resource Management Sector accountable to the Chief Executive Officer of the Corporation. According to the new structure of the Corporation four sectors, 19 branches and six sub branches located in different regions of the country; organized under Corporate Operation main Sector D/Chief Executive Officer and four support giving units led by Corporate Resource Management Sector D/Chief Executive Officer. And the remaining six corporate service giving units are accountable to the Chief Executive Officer

ኮርፖሬሽኑ 46 ትራክተሮችን ለተጠቃሚዎች አስረከበ

የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ከ151 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 46 ዱዝ-ፋር (DEUTZ-FAHR) ትራክተሮችንከጣሊያንሀገርበማስመጣትለተጠቃሚዎችበሽያጭ አስረክቧል፡፡ ከ110 እስከ 180 የፈረስ ጉልበት ያላቸው እነዚህ ትራክተሮች በሽያጭ የቀረቡት ለአማራ ክልል ግብርና ቢሮ፣ ለሲዳማ ክልል እርሻ እና የተፈጥሮ ሃብት ቢሮ እንዲሁም ለእንጅባራ፣ ደብረ ብርሃን እና ጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች፤ ለአጋርፋ ግብርና ኮሌጅ እና በእርሻ ሥራ ላይ ለተሰማሩ ባለሃብቶች ነው፡፡ ትራክተሮቹ የ2021 እና 2022 ምርት በመሆናቸው ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ ከማሟላታቸው ባሻገር ለሀገራችን የአየር ንብረትና የመሬት አቀማመጥ ተስማሚ ስለመሆናቸው ተጠቃሚዎች ይመሰክራሉ፡፡ ከዚህ አኳያ ትራክተሮቹ በሀገራችን ሜካናይዝድ እርሻን ለማስፋፋት፣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እና የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖራቸው ይታመናል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ኮርፖሬሽኑ የተጨማሪ 12 ዱዝ-ፋር ትራክተሮች ግዥ የፈጸመ ሲሆን፣ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ሀገር ውስጥ ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በቀጣይም የአመራረት ዘዴን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ ዘመናዊ፣ አስተማማኝና ጥራት ያላቸውን የእርሻ መሣሪያዎች እስከ መለዋወጫቸው ከውጭ ሀገር በማስመጣት ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡ በሌላ በኩል ኮርፖሬሽኑ ለሚያቀርባቸው ትራክተሮች ከሽያጭ በኋላ የጥገና፣ የቴክኒክ ሞያ ሥልጠና እንዲሁም መለዋወጫዎችን የማቅረብ አገልግሎቶችን ይሰጣል፡፡ እንዲሁም ከግብርና ማሳደጊያዎች ግብዓት እና መሣሪያዎች አቅርቦት በተጨማሪ ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ የሚዘልቅ የተቀናጀ የግብርና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ተደራሽ እያደረገ ይገኛል፡፡ በተጨማሪ የእርሻና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ኪራይ፣ የደረቅ ጭነት ትራንስፖርት፣ የተሽከርካሪዎች ጥገና፣ የዘር ብጠራ እና የማማከር ሥራ በኮርፖሬሽኑ የሚሰጡ ሌሎች አገልግሎቶች ናቸው፡፡ በአምስት ትላልቅ የልማት ደርጅቶች ውህደት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 368/2008 መሠረት ታህሳስ 2008 ዓ.ም የተቋቋመው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ለግብርና ምርትና ምርታማነት እድገት እና ለዘርፉ መዘመን የላቀ አስተዋጽዖ ያላቸውን ምርጥ ዘር፣ የአፈር ማዳበሪያ፣ አግሮኬሚካልና የኬሚካል መርጫ መሣሪያዎችን እንዲሁም የእርሻ መሣሪያዎችን ከነመለዋወጫቸው ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ ይገኛል።

ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!

“ለኮርፖሬሽኑ ምርጥ ዘር ለሚያባዙ ባለሃብቶች የምናደርገውን ድጋፍ አጠናክረን እንቀጥላለን” የኢግሥኮ ዋና ሥራ አስፈጻሚ

ከኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ጋር ውል ገብተው ምርጥ ዘር እያባዙ ለሚገኙ ባለሃብቶች ኮርፖሬሽኑ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ይህን የገለጹት፣ በምስራቅ ባሌ ዞን  በኮንትራት እርሻ ለኮርፖሬሽኑ የምርጥ ዘር እያባዙ ከሚገኙ ባለሃብቶችና የባለድርሻ አካላት ጋር  በቢሾፍቱ ያቱ ሆቴል ግንቦት 28/2014 ዓ.ም. በተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ ነው፡፡ “እናንተ ዘር የምታባዙት ለእኛ በመሆኑ ከራሳችን እርሻ ለይተን አናያችሁም” ያሉት አቶ ክፍሌ፣ ለዚህም አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ እና በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ ነን ብለዋል፡፡ ባለሃብቶቹ በበኩላቸው ምርጥ ዘር የማባዛት ሥራን ከኮርፖሬሽኑ ጋር በትብብር እየሰሩና በተቋሙም ድጋፍ እየተደረገላቸው ስለመሆኑ አስታውሰው፣ በቀጣይም ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡ አክለውም በአፈር ማዳበሪያ፣ በመስራች ዘር እና አግሮኬሚካሎች አቅርቦት ላይ ያጋጠሙ ችግሮች እንዲስተካከሉ እንዲሁም የሰብል ዝርያዎች ምርታማነት እየቀነሰ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ አዳዲስ የተሻሻሉ የሰብል ምርጥ ዘሮች እንዲቀርብላቸው ጠይቀዋል፡፡

 የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከባለሃብቶች ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ፣ የተጠየቁ የግብርና ግብዓቶችን በቀጣይ ጊዜያት እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል። በኮርፖሬሽኑ የኦፕሬሽን ዐቢይ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፈለቀ ገዛኸኝ በመድረኩ ባቀረቡት ገለጻ፣ ኮርፖሬሽኑ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን የምርጥ ዘር አቅርቦት እየሸፈነ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ ከዚህ ውስጥ ኮርፖሬሽኑ አብዛኛውን ዘር በሰፋፊ የመንግሥት እና ባለሃብቶች እርሻዎች እንዲሁም በአርሶ አደር ማሳ ላይ በትብብር በማምረት ለተጠቃሚዎች እንደሚያቀርብ አስታውቀዋል፡፡ ከዚህ አኳያ በዘንድሮ የሰብል ዘመን ኮርፖሬሽኑ ከ36 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያለው ምርጥ ዘር በብድር ለባለሃብቶች መስጠቱን እንዲሁም የሞያና ሌሎች ድጋፎችን ማድረጉን በኮርፖሬሽኑ የኢትዮጵያ ምርጥ ዘርና ደን ውጤቶች አቅርቦት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዘነበ ወልደሥላሴ ተናግረዋል። የኮፈሌ ቅ/ጽ/ቤት ሓላፊ አቶ ቡሽራ መሐመድ በበኩላቸው፣ ቅርንጫፉ ከምርጥ ዘር አባዥ ባለሃብቶች ጋር በመተባበር በመጪው የመኸር ወቅት 5 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት በዘር በመሸፈን ከ131 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለማምረት አቅዶ አየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኮርፖሬሽኑ በኮንትራት እርሻ በተለያዩ አካባቢዎች በባለሃብቶች መሬት ከሚያባዛው ምርጥ ዘር ውስጥ  በምስራቅ ባሌ ዞን የሚያባዛው ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው አቶ ቡሽራ ጠቁመዋል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የምስራቅ ባሌ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ እስማኤል ባስተላለፉት መልእክት፣ ኮርፖሬሽኑ በዞኑ ለሚያደርገው የግብርና ልማት በጋራ ከማቀድ ጀምሮ ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታውቀው፣ በዞኑ ያለውን የመስኖ ልማት በመጠቀም ለቆላማ አካባቢዎች ተስማሚ የሆኑ ምርጥ ዘር የማባዛት ሥራ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ አቅጣጫ አመላክተዋል። በመድረኩ ስለ ምርጥ ዘር አመራረት፣ አዘገጃጀትና ሥርጭት፤ የዘር ጥራት ቁጥጥር፣ መርሆዎችና ሂደት እንዲሁም የሀገሪቱ የምርጥ ዘር ፖሊሲ፣ ህግና ደንብን አስመልከቶ በባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ የኮፈሌ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ባዘጋጀው በዚህ የግማሽ ቀን የውይይት መድረክ ላይ የኮርፖሬሽኑ አመራሮችና ባለሞያዎች፤ የምስራቅ ባሌ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ፣ የዞኑ የግብርና እና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ሓላፊዎች፤ በምርጥ ዘር ብዜት የተሰማሩ ድርጅቶች እና ማህበራት እንዲሁም የአርዳይታ እና አጋርፋ የግብርና ቴክኒክና ሞያ ማሠልጠኛ ኮሌጆች ተገኝተዋል፡፡ በመድረኩ ማጠቃለያም በ2013/14 የምርት ዘመን ከኮርፖሬሽኑ ጋር በመተባበር በምስራቅ ባሌ ዞን በኮንትራት እርሻ በምርጥ ዘር ብዜት የላቀ አስተዋጽዖ ላበረከቱ የዘር አባዦችና የባለድርሻ አካላት የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀት ተሰጥቶአቸዋል። የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በራሱ እርሻዎች፣ በሰፋፊ የመንግሥት እና ባለሃብት እርሻዎች እንዲሁም በአርሶ አደር ማሳ ላይ ምርጥ ዘርን በጥራት እና በብዛት በማባዛት ለተጠቃሚዎች እያሰራጨ የሚገኝ የመንግሥት የልማት ድርጅት ነው፡፡

ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!

EABC Executive Management

   
  Mr. Kifle Woldemariam
Chief Executive Officer, CEO
አቶ ክፍሌ ወልደማሪያም
ዋና ሥራ አስፈፃሚ
 
 
Mr. Feleke Gezahegn
Corporate Operation, Deputy CEO
አቶ ፈለቀ ገዛህኝ
የኮርፖሬት ኦፐሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ
  Mr. Tensay Mecha
Corporate Resource Management Sector, Deputy CEO
አቶ ተንሳይ ሜጫ
የኮርፖሬት ሐብት ስራ አመራር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ
Mr. Zenebe Woldesilasie
Ethiopian Seed and Forest Products Supply Sector, Executive Officer
አቶ ዘነበ ወ/ሥላሴ
የኢትዮጵያ ምርጥ ዘር እና ደን ውጤቶች አቅርቦት ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ
Mr. Solomon Gebre
Agricultural Inputs Supply Sector, Executive Officer
አቶ ሰለሞን ገብሬ
የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ
Mr. Mengistu Kifle
Agricultural Equipment Supply and Mechanization Service Sector, Executive Officer
አቶ መንግስቱ ክፍሌ
የእርሻ መሣሪያዎች አቅርቦትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ
Mr. Asmamaw Gizachew
Acting Trucks Administration and Maintenance Sector, Executive Officer
አቶ አስማማው ግዛቸው
የተሸከርካሪዎች አስተዳደር ጥገና ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ
Mr. Asfaw Legesse
Corporate Research and Development Service, Head
አቶ አስፋው ለገሰ
የኮርፖሬት የጥናትና ምርምር አገልግሎት ኃላፊ ተወካይ
Mrs. Sinhiwot Getnet
Corporate Plan and Quality Management Service, Head
ወ/ሮ ሥነ ሕይወት ጌትነት
የኮርፖሬት ዕቅድና የአሰራር ሥርዓት ማሻሻያ አገልግሎት ኃላፊ
Mr. Gashaw Aychiluhim
Corporate Communication and Social Affairs Service, Head
አቶ ጋሻው አይችሉህም
የኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽንና ማህበራዊ ጉዳዮች አገልግሎት ኃላፊ
Mr. Alemayehu Siyoum
Corporate Audit and Risk Management Service, Head
አቶ አለማየሁ ስዩም
የኮርፖሬት ኦዲትና ስጋት ሥራ አመራር አገልግሎት ኃላፊ
Mr. Nuramin Sied
CEO office and Ethics Service Head
አቶ ኑራሚን ሰይድ
የዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት እና ስነ ምግባር አገልግሎት ኃላፊ
Mr. Feleke Engidashet
Corporate Legal Service, Head
አቶ ፈለቀ እንግዳሸት
የኮርፖሬት ህግ ጉዳዮች አገልግሎት ኃላፊ
Mr. Solomon Lemma
Corporate Human Resource Management, Manager.
አቶ ሰለሞን ለማ
የኮርፖሬት የሰው ሃብት ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ
Mrs Menbere Hailmariam
Corporate Finance Management, Manager
ወ/ሮ መንበረ ኃ/ማርያም
የኮርፖሬት ፋይናንስ ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ
Mr. Tesfaye Aklilu
Corporate Procurement and Asset Management, Manager
አቶ ተስፋዬ አክሊሉ
የኮርፖሬት የግዥና ንብረት አስተዳደር ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ
Mr. Kassahun Kebede
Advisor of the CEO
አቶ ካሳሁን ከበደ
የዋና ሥራ አስፈጻሚ አማካሪ

Management Team

Mr. Kifle Woldemariam
Chief Executive Officer, CEO
አቶ ክፍሌ ወልደማሪያም
ዋና ሥራ አስፈፃሚ
Mr. Feleke Gezahign
Corporate Operation, Vice CEO
አቶ ፈለቀ ገዛህኝ
የኮርፖሬት ኦፐሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ
Mr. Zenebe Woldesilasie
Ethiopian Seed and Forest Products Supply Sector, Executive Officer
አቶ ዘነበ ወ/ሥላሴ
የኢትዮጵያ ምርጥ ዘር እና ደን ውጤቶች አቅርቦት ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ
Mr. Solomon Gebre
Agricultural Inputs Supply Sector, Executive Officer
አቶ ሰለሞን ገብሬ
የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ ተጠባባቂ ሥራ አስፈጻሚ
Mr. Mengistu Kifle
Agricultural Equipment and Mechanization Service Sector Executive Officer
አቶ መንግስቱ ክፈሌ
የእርሻ መሣሪያዎችና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ
Mr. Bahriw Semere
Vehicles Administration and Maintenance Sector, Executive Officer
አቶ ባህሪው ሰመረ
የተሸከርካሪዎች አስተዳደር ጥገና ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ
Mr. Bahriw Semere
Vehicles Administration and Maintenance Sector, Executive Officer
አቶ ባህሪው ሰመረ
የተሸከርካሪዎች አስተዳደር ጥገና ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ
Mrs. Sinhiwot Getnet
Corporate Plan and Quality Management Service, Head
ወ/ሮ ሥነ ሕይወት ጌትነት
የኮርፖሬት ዕቅድና የአሰራር ሥርዓት ማሻሻያ አገልግሎት ኃላፊ
Mr. Gashaw Aychiluhm
Corporate Communication and Social Affairs Service, Head
አቶ ጋሻው አይችሉህም
የኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽንና ማህበራዊ ጉዳዮች አገልግሎት ኃላፊ
Mr. Alemayehu Siyum
Corporate Audit and Risk Management Service, Head
አቶ አለማየሁ ስዩም
የኮርፖሬት ኦዲትና ስጋት ሥራ አመራር አገልግሎት ኃላፊ
Mr. Tensay Mecha
CEO office and Ethics Service Head
አቶ ተንሳይ ሜጫ
የዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት እና ስነ ምግባር አገልግሎት ኃላፊ
Mr. Feleke Engidashet
Corporate Legal Service, Head
አቶ ፈለቀ እንግዳሸት
የኮርፖሬት ህግ ጉዳዮች አገልግሎት ኃላፊ
Mr. Tiku Biru
Corporate Human Resource Management, Manager.
አቶ ትኩ ብሩ
የኮርፖሬት የሰው ሃብት ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ
Mrs Menbere Hailmariam
Corporate Finance Management, Manager
ወ/ሮ መንበረ ኃ/ማርያም
የኮርፖሬት ፋይናንስ ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ
Mr. Tesfaye Feyisa
Corporate Procurement and Asset Management, Manager
አቶ ተስፋዬ ፈይሳ
የኮርፖሬት የግዥና ንብረት አስተዳደር ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ
Asaye Addise
Corporate Information and Communication, Manager
አቶ አሳዬ አዲሴ
የኮርፖሬት ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ