የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ ገብቷል – ዶክተር ግርማ አመንቴ

(አዲስ አበባ፣ ጥር 10 ቀን 2016 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) የግብርና ሚኒስትሩ ዶ/ር ግርማ አመንቴ እና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትሩ ዶ/ር ዓለሙ ስሜ በ2016/17 ምርት ዘመን የአፈር ማደበሪያ አገባብ ዕቅድ ክንውን ላይ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በተያዘው የምርት ዘመን የግብርና ሚኒስቴር 23 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት አቅዶ ከክልሎች በተሰበሰበው የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎት መሰረት 19.4 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት 930 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ተድርጎ ግዥ እየተፈጸመ መሆኑን ዶ/ር ግርማ አመንቴ ተናግረዋል፡፡ ግዥ ከተፈፀመው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥም 5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ ገብቷል ብለዋል ሚኒስትሩ፡፡ በምርት ዘመኑም ከሚገዛው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ 25 በመቶው ለመስኖ ስንዴ ልማት፣ 20 በመቶው ለበልግ እርሻ ስራ እንዲሁም ቀሪው 55 በመቶ ለመኸር እርሻ ጥቅም ላይ እንደሚውል አብራርተዋል፡፡ አርሶና አርብቶ አደሩም የሚቀርብለትን የአፈር ማዳበሪያ በአግባቡ በመጠቀም የግብርና ልማት ስራዎችን እንዲያከናውኑ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የአፈር ማዳበሪያ የማጓጓዙን ስራ ለማከናወን ከ10 ሺህ በላይ የየብስ ተሸከርካሪዎችን በማሰማራት እየተሰራ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ከ16 በላይ የባቡር ማጓጓዣዎችንም በመጠቀም ወደብ የደረሰውን የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ የማስገባት ስራ እየተሰራ መሆኑን ዶ/ር ዓለሙ ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም የ2016/17 በጀት ዓመት የአፈር ማደበሪያ አገባብ ዕቅድ እና ክንውን ላይ የስትሪንግ ኮሚቴ ውይይት ተካሂዷል፡፡
ካሜራ፡- ያሬድ አሰፋ
ዘጋቢ፥- ሰለሞን ደምሰው

ኮርፖሬሽኑ 10 አጭዶመውቂያዎችንተረከበ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 11/ 2016 ዓ.ም. (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከቻይና ያስመጣቸውን ‘ዙምላየን’ በመባል የሚታወቁ 10 አጭዶ መውቂያዎችን (combine harvesters) ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2016 ተረከበ፡፡ የአጭዶ መውቂያዎቹን ቁልፍ የዙምላየን ካምፓኒ ተወካይ ሚስተር አሊን ኪን ለኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም አስረክበዋል፡፡

በርክክቡ ወቅት አቶ ክፍሌ እንደተናገሩት፣ የቻይና የእርሻ እና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች አምራች ኩባንያ ከሆነው ዙምላየን ጋር ኮርፖሬሽኑ የንግድ ስምምነት በመፈጸም ለመጀመሪያ ጊዜ አጭዶ መውቂያ መሣሪያዎችን ለአርሶ አደሮች፣ በግብርና ሥራ ለተሰማሩ ድርጅቶች እና ባለሀብቶች ማቅረቡን ገልጸዋል። አጭዶ መውቂያዎቹ ብልሽት ሲያጋጥማቸው በቀላሉ የሚጠገኑ፣ ለአያያዝና አጠቃቀም ምቹ እና ለሀገራችን የአየር ንበረትና የመሬት አቀማመጥ ተስማሚ በመሆናቸው በአብዛኛው ተጠቃሚዎች ዘንድ ተመራጭነት እንደሚኖራቸው አቶ ክፍሌ አስታውቀዋል፡፡

የዙምላየን ተወካይ አሊን ኪን በበኩላቸው፣ አጭዶ መውቂያዎቹን ለማስተዋወቅ በመገኘታቸው ክብር እንደሚሰማቸው ጠቁመው፣ ዙምላየን ኩባንያ በቻይና ግንባር ቀደም የኮንስትራክሽን እና እርሻ መሣሪያዎች አምራች መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ኩባንያቸው የእርሻ መሣሪያዎችን በማቅረብ ረገድ የስኬት ታሪክ ያለው መሆኑን አንስተው፣ ከኮርፖሬሽኑ ጋር ከሽያጭ በኋላ በተለያዩ የቴክኒክ እና ሞያ ድጋፎች አብረው እንደሚሰሩና በዚህም ስኬታማ እንደሚሆኑ አስረድተዋል፡፡ በሌላ በኩል አጭዶ መውቂያዎቹ በምርት መሰብሰብ ወቅት የሚከሰት ብክነትን በማስቀረት ምርታማነትን እንደሚጨምሩም ተናግረዋል፡፡ ከርክክቡ ቀጥሎ የአጭዶ መውቂያዎቹ የትውውቅ ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን፤ አጭዶ መውቂያው ስንዴ፣ በቆሎ፣ ጤፍ፣ አኩሪ አተር እና ሌሎች የሰብል አይነቶችን ማጨድና መውቃት እንደሚችል በባለሞያዎች ተብራርቷል። በአንድ ጊዜ እስከ አራት ሜትር ስፋት ያለው ሰብል አጭዶ መውቃት እንደሚችል የተነገረለት ዙምላየን አጭዶ መውቂያ፣ 25 ኩንታል የመያዝ አቅም ያለው ጎተራ/ቋት እንዳለው በትውውቁ ላይ ተገልጿል። በዋናው መሪያ ቤት ግቢ በተካሄደው የርክክብ ሥነ ሥርዓት ላይ ከዙምላየን የመጡ የቴክኒክ ባለሞያዎች፣ የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባል፣ የሥራ መሪዎች፣ የመሠረታዊ የሠራተኛ ማኅበር ሰብሳቢ እና ሠራተኞች ተገኝተዋል፡፡ ከዙምላየን የመጡ የቴክኒክ ባለሞያዎች ከህዳር 7-8/2016 ዓ.ም ስለ አጭዶ መውቂያው ለኮርፖሬሽኑ ኦፕሬተሮችና መካኒኮች የቴክኒክ ሞያ ሥልጠና ሰጥተዋል፡፡ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የግብርና ግብዓቶችን እና የእርሻ መሣሪያዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች በማቅረብ፣ ከማሳ ዝግጅት እስከ ጎተራ የሚዘልቅ የተቀናጀ የሜካናይዜሽን አገልግሎት በመስጠት እንዲሁም አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ የሀገሪቷን ግብርና ለማዘመን እየሰራ ይገኛል። ኮርፖሬሽኑ በአሁኑ ወቅት የቼክ ሪፐብሊክ ስሪት የሆነውን ‘ዜቶር’ ትራክተር እና ሌሎች የእርሻ መሣሪያዎችን ከአውሮፓ እና ቻይና በማስመጣት ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡

የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የምርት መሰብሰብ ሥራ አስጀመሩ ለበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የሚውል ዘር እየተሰበሰበ ነው

አርዳይታ፣ ህዳር3/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአርዳይታ ቅድመ መስራች፣ መስራች እና የተመሰከረለት ዘር እርሻ ልማት የደረሰ ምርት የመሰብሰብ ሥራን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አስጀመሩ። ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ዛሬ ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም በአርዳይታ የዘር ማባዣ እርሻ ልማት ተገኝተው የምርት መሰብሰብ ሥራን አስጀምረዋል። የእርሻ ጣቢያው በ2015/16 የምርት ዘመን የስንዴ፣ ገብስ፣ ጎመን ዘር እና በቆሎ ሰብሎች 20 ዝርያዎችን ማባዛቱን የገለጹት አቶ ክፍሌ፣ በቅድመ መስራች፣ መስራች እና የተመሰከረለት ዘር ከተሸፈነው 3 ሺህ 69.32 ሄክታር መሬት ከ82 ሺህ ኩንታል በላይ ዘር እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል። ከሚሰበሰበው ዘር ውስጥ ለበጋ መስኖ ልማት የሚውል የስንዴ ዘር ዋነኛው መሆኑንም አክለው ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ በምርጥ ዘር አቅርቦት ፋና ወጊ የሆነው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በተለያዩ ክልሎች አምስት አካባቢዎች የቅድመ መስራች፣ መስራች እና የተመሰከረለት ዘር ማባዣ እርሻ ልማት ጣቢያዎችን (አርዳይታ፣ ጎንዴ ኢተያ፣ ጊቤ፣ ቻግኒ እና ታማሻሎ) በማቋቋም እንዲሁም በሰፋፊ የመንግሥትና የግል እርሻዎች እና በክላስተር በተደራጁ አርሶ አደሮች ማሳዎች በኮንትራት በመስራት በአማካይ በ15 ሺህ ሄክታር መሬት የ22 ሰብሎችን 78 ዝርያዎች እያባዛ በዓመት ከ350 ሺህ ኩንታል በላይ ዘር ለተጠቃሚዎች እያቀረበ ይገኛል፡፡ ይህም ኮርፖሬሽኑ በሀገር ደረጃ ካለው የምርጥ ዘር ፍላጎት ውስጥ ከ30 በመቶ በላይ የሚሆነውን ድርሻ እንዲያሟላ አስችሎታል፡፡ ኮርፖሬሽኑ በ2015/16 ምርት ዘመን በሦስት የዘር ደረጃዎች በእራሱ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻዎች፣ በሰፋፊ ኮንትራት አባዥዎች እና በክላስተር በተደራጁ አርሶ አደሮች ማሳዎች በዘር ከሸፈነው 20 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት 473 ሺህ 791 ኩንታል ዘር ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል። የሀገሪቷን ግብርና ለማዘመን በአንድ መስኮት የተሟላ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው ኮርፖሬሽኑ፣ የተለያዩ የግብርና ግብዓቶችንና የእርሻ መሣሪያዎችን ለተጠቃሚዎች ከማቅረቡ ባሻገር የተቀናጀ የግብርና ሜካናይዜሽን፣ የደረቅ ጭነት እንዲሁም ከሽያጭ በኋላ የቴክኒክና ሞያ፣ የምክርና የጥገና አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ ላይ ይገኛል።

“በአፈር ማዳበሪያ ግዥ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ለውጥ በመደረጉ ማዳበሪያ በመጠን፣ በጥራት፣ በተመጣጣኝ ዋጋ እና በጊዜ ለመግዛት እና ለማጓጓዝ ተችሏል” የግብርናሚኒስቴር “የማዳበሪያ ጉዳይ የሉዓላዊነት ጉዳይ በመሆኑ የእኛን አርበኝነት ይጠይቃል” የትራንስፖርትናሎ ጂስቲክስ ሚኒስቴር

አዲስአበባ፣ጥቅምት 30/ 2016 ዓ.ም. (ኢግሥኮ)፡- በአፈር ማዳበሪያ ግዥ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ለውጥ በመደረጉ ማዳበሪያ በመጠን፣ በጥራት፣ በተመጣጣኝ ዋጋ እና በጊዜ ለመግዛት እና ለማጓጓዝ መቻሉን  የግብርና ሚኒስትሩ ገለጹ። ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ይህን የገለጹት በአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ሥርጭት ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እና መፍትሔዎች ዙሪያ በአዳማ ኃይሌ ሪዞርት ሆቴል ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም በተደረገ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ነው፡፡በግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ትብብር በተዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንደተናገሩት፣ የማዳበሪያ ጉዳይ የሉዓላዊነት ጉዳይ በመሆኑ የአስፈጻሚዎችን አርበኝነት ይጠይቃል ብለዋል። ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ በማዳበሪያ አቅርቦት እና ሥርጭት ላይ ተዋንያን የሆኑ የፌዴራልና የክልል ተቋማት ተናበው በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። ከዚህ በኋላ መንግሥት በማዳበሪያ ሥርጭት ላይ ምንም አይነት የአፈጻጸም ክፍተት አይታገስም ያሉት አለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የ2016/17 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ እስከ ግንቦት ወይም ሰኔ 2016 ዓ.ም ድረስ ተጓጉዞ እንደሚጠናቀቅ አስታውቀዋል። የማዳበረያ ግዥ መጓተትን ለመፍታት ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ሥራ ላይ የነበረው የግዥ መመሪያ እንዲቀየር መደረጉን እና አሁን ላይ ማዳበሪያ ከአምራቾች በቀጥታ ግዥ፣ በውስን ጨረታ እና የመንግሥት ለመንግሥት ግዥ መፈጸም የሚቻልበት አሠራር መዘርጋቱን የተናገሩት ደግሞ የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ ቀድሞ በነበረው የአፈር ማዳበሪያ የግዥ ሥርዓት መሰረት የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የጨረታ ሥራውን ካከናወነ በኋላ የግብርና ሚኒስቴር ግዥውን ያጸድቅ እንደነበረና ይህም መጓተትን ፈጥሮ መቆየቱን አስታውሰዋል። አክለውም አዲሱ የግዥ መመሪያ የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ በግዥው ላይ ሙሉ ኃላፊነት ወስዶ ውሳኔ እንዲያሳልፍ ዕድል የሚሰጠው መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በአጠቃላይ በአፈር ማዳበሪያ ግዥ ላይ ከፍተኛ ለውጥ በመደረጉ ከግዥ ጋር የተያያዙ ችግሮች መፈታታቸው እና በዚህም ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የአፈር ማዳበሪያን ቀደም ብሎ መግዛት እና ማጓጓዝ መጀመሩን ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የ2015/16 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ሥርጭት አፈጻጸም እንዲሁም የ2016/17 የማዳበሪያ ግዥና ሥርጭት ያለበት ደረጃን በተመለከተ በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ኢንቨስትመንት እና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ገለጻ ቀርቧል። በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ ውይይቱን ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)  እና አለሙ ስሜ (ዶ/ር)  መርተውታል። በወቅቱ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ምላሽ ሰጥተዋል። በውይይቱ የግብርና ሚኒስቴር እና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፤ የክልል ግብርና እና የጸጥታ ቢሮ ኃላፊዎች፤ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን እና የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡                                

በግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ትብብር በተዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንደተናገሩት፣ የማዳበሪያ ጉዳይ የሉዓላዊነት ጉዳይ በመሆኑ የአስፈጻሚዎችን አርበኝነት ይጠይቃል ብለዋል። ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ በማዳበሪያ አቅርቦት እና ሥርጭት ላይ ተዋንያን የሆኑ የፌዴራልና የክልል ተቋማት ተናበው በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። ከዚህ በኋላ መንግሥት በማዳበሪያ ሥርጭት ላይ ምንም አይነት የአፈጻጸም ክፍተት አይታገስም ያሉት አለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የ2016/17 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ እስከ ግንቦት ወይም ሰኔ 2016 ዓ.ም ድረስ ተጓጉዞ እንደሚጠናቀቅ አስታውቀዋል። የማዳበረያ ግዥ መጓተትን ለመፍታት ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ሥራ ላይ የነበረው የግዥ መመሪያ እንዲቀየር መደረጉን እና አሁን ላይ ማዳበሪያ ከአምራቾች በቀጥታ ግዥ፣ በውስን ጨረታ እና የመንግሥት ለመንግሥት ግዥ መፈጸም የሚቻልበት አሠራር መዘርጋቱን የተናገሩት ደግሞ የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ ቀድሞ በነበረው የአፈር ማዳበሪያ የግዥ ሥርዓት መሰረት የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የጨረታ ሥራውን ካከናወነ በኋላ የግብርና ሚኒስቴር ግዥውን ያጸድቅ እንደነበረና ይህም መጓተትን ፈጥሮ መቆየቱን አስታውሰዋል። አክለውም አዲሱ የግዥ መመሪያ የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ በግዥው ላይ ሙሉ ኃላፊነት ወስዶ ውሳኔ እንዲያሳልፍ ዕድል የሚሰጠው መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በአጠቃላይ በአፈር ማዳበሪያ ግዥ ላይ ከፍተኛ ለውጥ በመደረጉ ከግዥ ጋር የተያያዙ ችግሮች መፈታታቸው እና በዚህም ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የአፈር ማዳበሪያን ቀደም ብሎ መግዛት እና ማጓጓዝ መጀመሩን ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የ2015/16 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ሥርጭት አፈጻጸም እንዲሁም የ2016/17 የማዳበሪያ ግዥና ሥርጭት ያለበት ደረጃን በተመለከተ በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ኢንቨስትመንት እና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ገለጻ ቀርቧል። በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ ውይይቱን ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)  እና አለሙ ስሜ (ዶ/ር)  መርተውታል። በወቅቱ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ምላሽ ሰጥተዋል። በውይይቱ የግብርና ሚኒስቴር እና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፤ የክልል ግብርና እና የጸጥታ ቢሮ ኃላፊዎች፤ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን እና የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ከውጭ ያስመጣቸውን ትራክተሮች ለፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሽያጭ አስረከበ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአውሮፓ ካስመጣቸው ‘ዜቶር’ ትራክተሮች ውስጥ ስምንት ትራክተሮችን ከእነተቀጽላቸው ‘ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ’ በመባል ለሚታወቅ ድርጅት በሽያጭ አስረከበ፡፡ ድርጅቱ ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ስምንት ትራክተሮችን፣ ስምንት ማረሻዎችን፣ ሦስት መከስከሻዎችን እና ሦስት መስመር ማውጫዎችን ከኮርፖሬሽኑ ገዝቷል።  ዛሬ ጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም በኮርፖሬሽኑ ዋና መስሪያ ቤት በተካሄደ የርክክብ ሥነ ሥርዓት ላይ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ለፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍስሀ እሸቱ (ዶ/ር) የትራክተሮቹን ቁልፍ አስረክበዋል፡፡

አቶ ክፍሌ በሥነ ሥርዓቱ ወቅት ይፋ እንዳደረጉት፣ በቀጣይ ለአማራ ክልል የ75 ዜቶር ትራክተሮች ርክክብ እንደሚደረግ ይጠበቃል። ኮርፖሬሽኑ የሀገሪቷን ግብርና ለማዘመን ጥራት ያላቸውን አስተማማኝ የእርሻ መሣሪያዎች ከአውሮፓና ከቻይና እያስመጣ ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ ይገኛል ያሉት አቶ ክፍሌ፣ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ የተረከባቸው የቼክ ሪፐብሊክ ስሪት የሆኑት ዜቶር ትራክተሮች የግብርና ምርታማነትን እንደሚያሳድጉ አስታውቀዋል፡፡ አክለውም ኮርፖሬሽኑ ለገበያ ለሚያቀርባቸው ዜቶር ትራክተሮች እና ሌሎች የእርሻ መሣሪያዎች ከሽያጭ በኋላ በዋናው መ/ቤት እና በክልሎች ባሉት 25 ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የጥገና አገልግሎት እንደሚሰጥ እና መለዋወጫዎች እንደሚያቀርብ  አረጋግጠዋል። የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍስሀ እሸቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው ድርጅታቸው ከኮርፖሬሽኑ ጋር ዘርፈ ብዙ የሥራ ግንኙነት እንዳለው ጠቁመው፣ በምርጥ ዘር ብዜት ከኮርፖሬሽኑ ጋር በጋራ እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ ኮርፖሬሽኑ ተደራሽ እና አስተማማኝ የሆነ አገልግሎት ስለሚሰጥ ትራክተሮቹን ከኮርፖሬሽኑ ለመግዛት እንደወሰኑ የገለጹት ፍስሀ እሸቱ (ዶ/ር)፣ በቀጣይም  ተጨማሪ ትራክተሮችን እንደሚገዙ ጠቁመዋል፡፡ በተመሳሳይ በመሬት ዝግጅት፣ በግብርና ግብዓት አቅርቦት እና በሌሎችም የዘርፉ አገልግሎቶች ከኮርፖሬሽኑ ጋር በትብብር መስራታቸውን እንደሚቀጥሉ አያይዘው ገልጸዋል፡፡ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በግብርና፣ በምግብ ማቀናበር፣ በሪል ስቴት፣ በችርቻሮ ንግድ እና በሌሎች መስኮች የተሰማራ ድርጅት ነው፡፡

ኮርፖሬሽኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኮንትራት እርሻ እያባዛ የሚገኘውን የድቃይ በቆሎ የተመሰከረለት የዘር ማሳ አስጎበኘ

ኮርፖሬሽኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኮንትራት እርሻ እያባዛ የሚገኘውን የድቃይ በቆሎ የተመሰከረለት የዘር ማሳ አስጎበኘ * የክልሉ መንግሥት ኮርፖሬሽኑ ላቀረበው ተጨማሪ የዘር ማባዣ መሬት ጥያቄ ምላሽ እንደሚሰጥ አስታውቋል ============================ አሶሳ፣ ጥቅምት 27/2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኮንትራት እርሻ  ከባለሀብት ጋር እያባዛ የሚገኘውን የድቃይ በቆሎ የተመሰከረለት የዘር ማሳ ለክልል፣ ዞን፣ ወረዳ እና ቀበሌ አመራሮች ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም አስጎበኘ። ከክልሉ ዋና ከተማ አሶሳ 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው የአሶሳ ዞን አብረሃሞ ወረዳ በተዘጋጀው የመስክ ጉብኝት እና በአሶሳ ከተማ ባምቡ ፓራዳይዝ ሆቴል በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ አቶ  አጥናፉ  አጎናፍር ፣ የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበከር ሀላፋ፣ የግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አጥናፉ ባቡር እንዲሁም ሌሎች የቢሮ፣ የዞን፣ የወረዳና የቀበሌ  አመራሮች እና የግብርና ባለሞያዎች ተገኝተዋል። በእንግዶች የተጎበኘው BH 546 በመባል የሚጠራው የድቃይ በቆሎ የተመሰከረለት ዘር ማባዣ ማሳ ሲሆን፣ ኮርፖሬሽኑ አቶ ሞላ ተመስገን ከተባሉ ባለሀብት ጋር በ146 ሄክታር መሬት ላይ በጋራ እያለመ የሚገኘው የኮንትራት እርሻ ነው። ይህንን እርሻ ጨምሮ ኮርፖሬሽኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በእሶሳ ዞን አምስት አካባቢዎች በ328 ሄክታር መሬት ላይ ድቃይ በቆሎ እና ድቃይ ያልሆነ በቆሎ የተመሰከረለት ዘር እያባዛ እንደሚገኝ እና 12 ሺህ ኩንታል ዘር እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ገልጸዋል። የክልሉ መንግሥት ለኮርፖሬሽኑ የዘር ማባዣ 1500 ሄክታር መሬት መፍቀዱን ያስታወሱት አቶ ክፍሌ፣ በሀገሪቷ እና በክልሉ ካለው የዘር ፍላጎት አንጻር ተጨማሪ 3500 ሄክታር የዘር ማባዣ መሬት አሶሳ ዞን ላይ እንዲሰጣቸው የክልሉን መንግሥት ጠይቀዋል። “ተጨማሪ መሬት ካገኘን በክልሉ የግብርና ግብዓት አቅርቦት እና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል እናቋቁማለን” ያሉት አቶ ክፍሌ፣ የማዕከሉ መቋቋም በክልሉ እና በአቅራቢያው የሚገኙ አርሶ አደሮች እና በግብርና ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች የግብርና ግብዓቶችን፣ የእርሻ መሣሪያዎችን እና መለዋወጫዎችን እንዲሁም የሜካናይዜሽን፣ የጥገና፣ የምክር እና የቴክኒክ ሞያ አገልግሎቶችን በቅርበት ለማግኘት እንደሚያስችላቸው አስረድተዋል። በኮርፖሬሽኑ ለቀረበው ተጨማሪ የዘር ማባዣ መሬት ጥያቄ የክልሉ መንግሥት ምላሽ እንደሚሰጥ የግብርና ቢሮ ኃላፊው አቶ ባበከር ሀላፋ አስታውቀዋል። በጉብኝቱ ላይ የተገኙት በአሶሳ ዞን የአብረሃሞ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አቡዱላጢፍ አፉዲ፣ ኮርፖሬሽኑ በክልሉ ውስጥ የሚታየውን የዘር ችግር ለመቅረፍ የሚያደረገውን ጥረት አድንቀው፣ ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። አክለውም ኮርፖሬሽኑ ትራክተሮች እና የግብርና ግብዓቶችን በስፋት ካቀረበላቸው በወረዳ ደረጃ የተሻለ ውጤት እንደሚያመጡ ገልጸዋል።  የመስክ ጉብኝቱ እና የውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፣ ኮርፖሬሽኑ በአዘጋጀው መርሀ ግብር ልምድ እንዳገኙ እና ስለ ኮርፖሬሽኑም የሥራ እንቅስቃሴ ግንዛቤ እንደጨበጡ ተናግረዋል። ኮርፖሬሽኑ በክልሉ ውስጥ የልማት እንቅስቃሴ ማካሄዱ የክልሉን ግብርና በማዘመን የአርሶ አደሩን የግብዓት ችግር ለመቅረፍ እንደሚረዳም አመልክተዋል። በመስክ ጉብኝቱ ወቅት ቴክኒካዊ ማብራሪያ የሰጡት  አቶ በሊና ብርሃኑ በኮርፖሬሽኑ የነቀምት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እንዳስረዱት፣ BH 546 የድቃይ በቆሎ የተመሰከረለት ዘር ከነባር ዝርያዎች በተሻለ ከፍተኛ ምርት ከመስጠቱ ባሻገር በሽታን የመቋቋም አቅሙ ከፍተኛ ነው። የኮርፖሬሽኑን አጠቃላይ ገጽታ በተመለከተም የኮርፖሬት ኦፕሬሽን ዐቢይ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፈለቀ ገዛኸኝ ለተሳታፊዎች ገለጻ አድርገዋል። በወቅቱ በተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በሀገር ደረጃ በምርጥ ዘር አቅርቦት ፋና ወጊ የሆነው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን፣ በተለያዩ ክልሎች የራሱን አምስት የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻ ልማት ጣቢያዎችን በማቋቋም እንዲሁም በሰፋፊ የመንግሥትና የግል እርሻዎች እና በክላስተር በተደራጁ አርሶ አደሮች ማሳ በኮንትራት በመስራት በአጠቃላይ በ15 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የ22 ሰብሎችን 78 ዝርያዎች እያባዛ በዓመት ከ350 ሺህ ኩንታል በላይ ዘር ለተጠቃሚዎች እያቀረበ ይገኛል፡፡ ይህም በሀገር ደረጃ ካለው የምርጥ ዘር ፍላጎት ውስጥ ከ30 በመቶ በላይ የሚሆነውን ድርሻ እንዲያሟላ አስችሎታል፡፡
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!

ኮርፖሬሽኑ ከአውሮፓ ከሚያስመጣቸው 75 ትራክተሮች ውስጥ 59ኙን ተረከበ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22/2016 ዓ.ም. (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአውሮፓ ከሚያስመጣቸው 75 ትራክተሮች ውስጥ 59ኙን ተረከበ።

በኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎች አቅርቦት፣ ማርኬቲንግና ሽያጭ መምሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ቶሎሳ እንዳስታወቁት፣ ኮርፖሬሽኑ የሀገሪቷን ግብርና ለማዘመን የሚያስችሉ የእርሻ መሣሪያዎችን ከእነተቀጽላቸው ከአውሮፓ እና ከቻይና እያስመጣ ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ከ110 እስከ136 የፈረስ ጉልበት ያላቸውን  ‘ዜቶር’ በመባል የሚታወቁ ትራክተሮችን ከቼክ ሪፐብሊክ እያስመጣ መሆኑን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፣ ከታዘዙ 75 ትራክተሮች ውስጥ እስከአሁን 59ኙን መረከባቸውን አስታውቀዋል፡፡ ቀሪዎቹ 16 ትራክተሮችም በቅርቡ  ወደ ሀገር ውስጥ እንደሚገቡ ተናግረዋል፡፡

ዜቶር ትራክተር ላይ የቴክኒክ ብልሽት ቢያጋጥም መለስተኛ የእጅ መሣሪያዎችን በመጠቀም በቀላሉ መጠገንና ማስተካከል እንደሚቻልም አስረድተዋል። ኮርፖሬሽኑ ትራክተሮችን ከማቅረብ ባሻገር ከሽያጭ በኋላ ለደንበኞች የቴክኒክና ሞያ ሥልጠና፣ የጥገና እና የምክር አገልግሎቶች አዲስ አበባ በሚገኘው የቴክኒክና ሞያ ማሠልጠኛ ማዕከል እና በቅርንጫፎቹ እየሰጠ ይገኛል፡፡

ኮርፖሬሽኑ የአርሶ አደሮች እና የባለሀብቶች ሰብል እየሰበሰበ ነው

ለመተሃራ ስኳር ፋብሪካ 700 ሄክታር የሸንኮራ አገዳ ማሳ እያዘጋጀ ይገኛል
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23/2016 ዓ.ም. (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአርሶ አደሮችን፣ በግብርና ሥራ የተሰማሩ ባለሀብቶችን እና የተለያዩ ድርጅቶችን የደረሰ ሰብል በተመጣጣኝ ዋጋ እየሰበሰበ ነው፡፡በኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎች እና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ ክፍሌ እንደገለጹት፣ ኮርፖሬሽኑ ከጥቅምት 2016 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ በሞጆ እና ሄረሮ ዙሪያ ለሚገኙ አርሶ አደሮች እና ባለሀብቶች የሰብል መሰብሰብ ሥራ እያከናወነ ይገኛል፡፡የሀገሪቱ የግብርና ምርት ሙሉ በሙሉ እስኪሰበሰብ ድረስ ኮርፖሬሽኑ አገልግሎቱን እንደሚቀጥል የተናገሩት አቶ መንግሥቱ፣ ከቀጣዩ ሳምንት ጀምሮ በጎጃም የአየሁ እርሻ ልማት የደረሰ ሰብል እንደሚሰበሰብ ተናግረዋል፡፡እንደ ሥራ አስፈጻሚው ማብራሪያ፣ ኮርፖሬሽኑ በ10 አጭዶ መውቂያ መሣሪያዎች የሰብል መሰብሰብ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ አገልግሎቱን ለማጠናከር ተጨማሪ 10 አጭዶ መውቂያዎችን ከውጭ አስመጥቶአል።

አቶ መንግሥቱ ክፍሌ

በሌላ በኩል ኮርፖሬሽኑ የመተሃራ ስኳር ፋብሪካን ነባር የሸንኮራ አገዳ በማስወገድ ለአዲስ የሸንኮራ አገዳ ተከላ 700 ሄክታር መሬት እያዘጋጀ መሆኑን አቶ መንግሥቱ አክለው አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በክልሎች ካሉት 25 ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ውስጥ የሞጆ፣ ሄረሮ እና ቡሬ ጣቢያዎች በዋናነት የተቀናጀ የግብርና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ለማስፋፋት እና ለማጠናከር የተቋቋሙ ናቸው፡፡