
የኮርፖሬሽኑ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ገለጸ
የኮርፖሬሽኑ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ገለጸ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 21/2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ገለጸ።
ቦርዱ ይህን የገለጸው፣ በግብርና ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ ሚያዝያ 21 ቀን 2017 ዓ.ም የኮርፖሬሽኑ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት ነው።በዚሁ ወቅት የግብርና ሚኒስትር እና የኮርፖሬሽኑ የቦርድ ሰብሳቢ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)፣ ተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት የገቢና ትርፍ ዕቅዱን በቀሪዎቹ ሁለት ወራት እንዲያሳካ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም በበኩላቸው፣ ኮርፖሬሽኑ እንደ ባለፉት ዓመታት የዘንድሮውን በጀት ዓመት የገቢና የትርፍ ዕቅድ ሙሉ በሙሉ እንደሚያሳካ ተናግረዋል። ዕቅዱን ለማሳካትም የኮርፖሬሽኑ የዋና መ/ቤት የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ከመጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከመደበኛ ሥራቸው በተጨማሪ በወር ሁለት ቅዳሜ ቀናትን በሥራ ለማሳለፍ ተስማምተው ደንበኞችን በማገልገል ላይ እንደሚገኙ አብራርተዋል።
በተመሳሳይ በተቋሙ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የቅዳሜ ሥራ መደበኛ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ክፍሌ፣ በቀጣዮቹ ሁለት ወራት ቀሪ የኦፕሬሽን ሥራዎችን በጥብቅ ዲሲፕሊን በመምራት፣ ገቢን በመጨመርና ወጪን በመቀነስ የኮርፖሬሽኑን ዕቅድ ማሳካት ይቻላል ብለዋል።
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!





ስለ እኛ
ምስረታ
የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) በግብርናው ዘርፍ ከ30 እስከ 40 ዓመት ድረስ በተናጠል አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ አምስት ነባር ድርጅቶችን (የኢትዮጵያ ምርጥ ዘር ድርጅት፣ የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅራቢ ድርጅት፣ የእርሻ መሣሪያዎችና የቴክኒክ አገልግሎት አክሲዮን ማኅበር፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ድርጅት እና የተፈጥሮ ሙጫ ምርትና ገበያ ድርጅት) በማዋሃድ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 368/2008 መሠረት ታህሳስ 2008 ዓ.ም የተቋቋመ መንግሥታዊ የልማት ድርጅት ነው፡፡
ተጠሪነት
በግሉ ዘርፍና በተደራጁ ማኅበራት የማይሸፈኑ የገበያ ክፍተቶች ውስጥ የድርሻውን በመውሰድ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን በማከናወን ላይ የሚገኘው ኮርፖሬሽኑ ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሲሆን፣ በሥራ አመራር ቦርድ ይመራል፡፡
የተቋቋመበት ዓላማ
የተቋቋመበት ዓላማ ለግብርና ምርትና ምርታማነት ዕድገት አስተዋጽዖ የሚያደርጉ እና ለዘመናዊ እርሻና ለአግሮ ኢንዱስትሪ መስፋፋት መሠረት የሚሆኑ ቴክኖሎጂዎችን እና ግብዓቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ በማድረግ ሀገራዊ ልማትና ዕድገትን ለማፋጠን ነው፡፡
አደረጃጀት
የአርሶ አደሩ እና አርብቶ አደሩ አለኝታ የሆነው ኮርፖሬሽኑ በመንግሥት የተሰጠውን ተልዕኮ ከመወጣት አኳያ በሦስት ኮርፖሬት ዘርፎች፣ ዓላማ አስፈፃሚ በሆኑ አምስት የኦፕሬሽን ዘርፎች፣ በ15 ድጋፍ ሰጪ የሥራ ሂደቶች እንዲሁም በበርካታ ቅርንጫፎች እና በጣቢያዎች በተደራጀ መዋቅር በ1,397 ቋሚና በ250 ኮንትራት በድምሩ በ1,647 ሠራተኞች ግብርናን ለማዘመን እየሰራ ይገኛል፡፡
የአንድ መስኮት አገልግሎት
የአንድ መስኮት የተቀናጀ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው ኮርፖሬሽኑ፣ በተቀናጀ የግብርና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ የሚዘልቁ የግብርና ሥራዎችን ያከናውናል፡፡ በተጨማሪም ለግብርና መዘመንና ለምርታማነት እድገት የላቀ አስተዋጽዖ ያላቸውን ግብዓቶች (ምርጥ ዘር፣ ጠጣርና ፈሳሽ ማዳበሪያዎች፣ አግሮኬሚካሎች) እንዲሁም የእርሻ መሣሪያዎችን ከእነተቀጽላቸው እና መለዋወጫቸው በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች ያቀርባል፡፡
ከዚህ ባሻገር ኮርፖሬሽኑ ለደንበኞቹ እየሰጠ የሚገኘውን የአንድ መስኮት አገልግሎት የተሟላ ለማድረግ የምክር፣ የቴክኒክና ሞያ ሥልጠና፣ የዘር ብጠራ፣ የደረቅ ጭነት ትራንስፖርት እና የተሽከርካሪዎች ጥገና አገልግሎቶችን በዋና መ/ቤት እና በቅርንጫፎች ተደራሽ በማድረግ ላይ ነው።
ምርጥ ዘር
በሀገር ደረጃ በምርጥ ዘር አቅርቦት ፋና ወጊ የሆነው ኮርፖሬሽኑ፣ በተለያዩ ክልሎች የራሱን ስድስት የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻ ልማት ጣቢያዎችን በማቋቋም እንዲሁም በሰፋፊ የመንግሥትና የግል እርሻዎች እና በክላስተር በተደራጁ አርሶ አደሮች ማሳ በኮንትራት በመስራት በአጠቃላይ ከ20 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የ22 ሰብሎችን 90 ዝርያዎች እያባዛ በዓመት ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ዘር ለተጠቃሚዎች እያቀረበ ይገኛል፡፡ ይህም በሀገር ደረጃ ካለው የምርጥ ዘር ፍላጎት ውስጥ 30 በመቶ የሚሆነውን ድርሻ እንዲያሟላ አስችሎታል፡፡
በሌላ በኩል ኮርፖሬሽኑ በተለያዩ ክልሎች በአገኛቸው ተጨማሪ የእርሻ መሬቶች ዘር እያባዛ ሲሆን፣ ወደ ውጭ የሚላኩ ሰብሎችን ለማምረትም ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
የደን ውጤቶች
ኮርፖሬሽኑ የደን ውጤቶች የሆኑትን ሙጫ፣ እጣን፣ ከርቤና አበከድ በማምረት እና በግዥ በማሰባሰብ አበጥሮ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ ጭምር በማቅረብ በዓመት በሚሊየን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሪ በማስገኘት ላይ ነው፡፡
ተቋሙ እነዚህን ምርቶች የሚሰበስበው በዘርፉ ከተሰማሩ ማኅበራትና ግለሰቦች በግዥ መልክ ሲሆን፣ የደን ውጤቶቹ በአብዛኛው በትግራይ፣ በአማራ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልሎች ቆላማ አካባቢዎች ይገኛሉ፡፡
ማዳበሪያ፣ አግሮኬሚካልና የእንስሳት መድኃኒት
ኮርፖሬሽኑ በሀገር ውስጥ ብቸኛ የጠጣር የአፈር ማዳበሪያ አስመጪ ሲሆን፣ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የአፈር ማዳበሪያዎች (በጠጣርና በፈሳሽ መልክ)፣ ጸረ አረም፣ ጸረ ነፍሳትና ጸረ ፈንገስ ኬሚካሎች እና የእንስሳት መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ላይ ነው፡፡
የእርሻ መሣሪያዎች
ኮርፖሬሽኑ ለሀገሪቱ መልክአ ምድር እና የአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ዘመናዊና ጥራት ያላቸውን ትራክተሮችና ተቀጽላዎች/implements – ማረሻ፣ መከስከሻ፣ መስመር ማውጫ፣ ዘር መዝሪያ፣ ማዳበሪያ መበተኛ…/፣ ኮምባይን ሀርቨስተር እንዲሁም የኮንስትራክሽን እና የኬሚካል መርጫ መሣሪያዎችና መለዋወጫዎችን ያቀርባል።
የሜካናይዜሽን አገልግሎት
የተቀናጀ የግብርና ሜካናይዜሽን አገልግሎትን በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች ተደራሽ በማድረግ የሚታወቀው ኮርፖሬሽኑ በግብርናው ዘርፍ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች፣ ከፊል አርብቶ አደሮች፣ ባለሃብቶች፣ የልማት ድርጅቶች ወዘተ ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ የሚዘልቁ የግብርና ሥራዎችን ያከናውናል፡፡
የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል
ኮርፖሬሽኑ ለካፒታል ፕሮጀክት በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የዘር ማበጠሪያና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ተደራሽ ባልሆነባቸው ክልሎች የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ለማቋቋም እየሰራ ነው፡፡ ለአብነት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በቦንጋ ከተማ የአስገነባውን ግዙፍ ማዕከል መጥቀስ ይቻላል፡፡ በተመሳሳይ ይህን መሰል ማዕከል በሌሎች ክልሎችም ለማስፋፋት የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፡፡
የእርሻ መሣሪያዎችን የመገጣጠም ሥራ
የግብርና ሜካናይዜሽንን በማስፋፋት ረገድ ኮርፖሬሽኑ አዳዲስ የእርሻ መሣሪያዎችን ታዋቂ ከሆኑ የአውሮፓ እና የቻይና አምራች ኩባንያዎች በማስመጣት እና ባለው ወርክሾፕ በሂደት ሙሉ በሙሉ ገጣጥሞ ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ ከውጭ ኩባንያዎች ጋር በሽርክና መስራት የሚችልበትን ስምምነት እያደረገ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ተቋሙ የእርሻ መሣሪያዎችን በከፊል የመገጣጠም ሥራ እያከናወነ ይገኛል፡፡
የደረቅ ጭነት ትራንስፖርት እና የተሽከርካሪዎች ጥገና አገልግሎቶች
ኮርፖሬሽኑ ከባድ ተሽከርካሪዎችን በማሰማራት ለውስጥ እና ለውጭ ደንበኞች የግብርና ግብዓቶችን እና የእርሻ መሣሪያዎችን እንዲሁም ሌሎች የደረቅ ጭነቶችን የማጓጓዝ አገልግሎት ይሰጣል፡፡
በሌላ በኩል ለውስጥ እንዲሁም ለተለያዩ የግልና የመንግሥት ተቋማት ደንበኞች የተሽከርካሪዎች የቅድመ መከላከል እና የብልሽት ጥገና አገልግሎት ይሰጣል፡፡
በተጨማሪም ለከባድ እና ቀላል ተሽከርካሪዎች ዓመታዊ የቴክኒክ ብቃት ማረጋገጫ ምርመራ/ቦሎ/ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡
የዓመታዊ ሽያጭ፣ ትርፍና የተፈቀደ ካፒታል እድገት
ኮርፖሬሽኑ ባለፉት ዓመታት በሀገራዊ የግብርና ዘርፍ የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ እና ለሦስተኛ ጊዜ በአዘጋጀው የተቋሙ ስትራተጂክ ዕቅድ (ከ2016-2020 ዓ.ም) እየተመራ ውጤትን መሰረት ያደረገ የዕቅድ አፈጻጸም ምዘና ሥርዓትን (BSC) የለውጥ መሣሪያ አድርጎ ወደ ሥራ በመግባቱ፣ በየዓመቱ የሂሳብ መግለጫ በIFRS ደረጃዎች መሰረት በወቅቱ ሂሳብ በመዝጋቱና በማስቀጠሉ እንዲሁም የISO 9001፡2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን በመተግበሩ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ ችሏል፡፡
በዚህም ዓመታዊ ገቢውን ሲቋቋም ከነበረበት ከ1.4 ቢሊዮን ብር ወደ 10.12 ቢሊዮን ብር እንዲሁም ከታክስ በፊት ትርፉን ከ45.6 ሚሊዮን ብር ወደ 1.8 ቢሊዮን ብር ማሳደግ ችሏል፡፡ ከዚህ የተነሳ ኮርፖሬሽኑ በየዓመቱ ምርቱን እያሳደገ እና አገልግሎቶቹን ይበልጥ ተደራሽ እያደረገ በመቀጠሉ እንዲሁም ትርፋማ ሆኖ በመዝለቁ ምክንያት ሲቋቋም በመንግሥት የተፈቀደለትን 2.44 ቢሊዮን ብር ካፒታል በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ በማሟላት አሁን ላይ የተፈቀደ ካፒታሉን ወደ 7 ቢሊዮን 564 ሚሊዮን ብር ማሳደግ ችሏል፡፡ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎም የተቋሙን ካፒታል በድጋሚ ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡
ማኅበራዊ ኃላፊነት
ማኅበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት ረገድም ኮርፖሬሽኑ በየዓመቱ በአማካይ ለ2500 ዜጎች ጊዜያዊ የሥራ እድል የሚፈጥር ሲሆን፣ ከሚያገኘው የተጣራ ትርፍ ላይም በየዓመቱ ለማኅበራዊ አገልግሎት በጀት በመመደብ በምርጥ ዘር ማባዣ እርሻ ልማት አካባቢዎች ለሚገኘው ማኅበረሰብ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በመንግሥት ለሚቀርብለት የተለያዩ የድጋፍ ጥሪዎች እና የስፖንሰርሺፕ ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ሲሰጥ ቆይቷል፤ አሁንም አቅም በፈቀደ መጠን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡
በዚህም በበጎ አድራጎት ሥራዎች በእርሻ ልማቱ አካባቢዎች ለሚገኘው ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት በመገንባት፣ መብራት በማስገባት፣ የአቅመ ደካሞችን መኖሪያ ቤቶች በማደስ፣ ለችግረኛ ቤተሰብ ልጆች የትምህርት መርጃ መሣሪያዎችን በመስጠት፣ ችግኞችን በመትከል እና ደም በመለገስ ድጋፍ እያደረገ ነው፡፡ በተመሳሳይ ለአካባቢው አርሶ አደሮች በአምስት በመቶ የዋጋ ቅናሽ ምርጥ ዘር በማቅረብ ለአርሶ አደሩ ያለውን አለኝታነት በማረጋገጥ ላይ ይገኛል፡፡
እውቅና እና ሽልማት
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ በሚያቀርባቸው የግብርና ግብዓቶችና በሚሰጣቸው የተቀናጁ አገልግሎቶች በገበያ ውስጥ ተመራጭ ስለመሆኑ የረጅም ዓመት ደንበኞቹ ምስክሮች ናቸው፡፡
ኮርፖሬሽኑ በግብርናው መስክ በአስመዘገበው አበረታች ውጤት የአቢሲኒያ ዓለም አቀፍ የጥራት ድርጅት ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለኢንደስትሪ ሽልማት ካጫቸው ከ57 ሺህ በላይ አምራች እና አገልግሎት ሰጪ የመንግሥት፣ የግል እና ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ውስጥ ከተመረጡ 50 ተቋማት አንዱ በመሆን መጋቢት 2015 ዓ.ም የመጀመሪያውን የኢንደስትሪ የከፍተኛ ክብር ሽልማት ተቀዳጅቷል፡፡
በተጨማሪም ኮርፖሬሽኑ በ2016 በጀት ዓመት ከ743 ሚሊየን ብር በላይ ግብር በመክፈል ለሁለተኛ ጊዜ በታማኝ ግብር ከፋይነት በፕላቲነም ደረጃ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እጅ ሽልማት ተቀብሏል፡፡
ከዚህ ባሻገር በ2015/16 የምርት ዘመን በሀገር አቀፍ ደረጃ በስንዴ ልማት ከሀገራዊ ፍላጎት እስከ ውጭ ገበያ አቅራቢነት በመሸጋገር ሂደት ለአበረከተው የላቀ አስተዋጽዖ እንዲሁም በ2016/17 ምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ ግዥ፣ አቅርቦት እና ሥርጭት እንዲሳለጥ ለተወጣው ከፍተኛ ድርሻም የእውቅናና የምስጋና የምስክር ወረቀት እና ዋንጫ አግኝቷል፡፡
በሌላ በኩል የኮርፖሬሽኑ የወንዶች የመረብ ኳስ ቡድን የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) በ2015 ዓ.ም በአዘጋጀው የስፖርት ውድድር ሻምፒዮን በመሆን ዋንጫ ተቀብሏል።
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!
About EABC
Establishment of EABC
The Ethiopian Agricultural Businesses Corporation (EABC) was established in December 2015 as a federal government public enterprise under Council of Ministers Regulation No. 368/2015, with an authorized capital of 2.44 billion birr.
The Corporation, governed by the Public Enterprises Proclamation No. 25/1992, was formed through the merger of five-state owned Enterprises; namely Ethiopian Seed Enterprise, Agricultural Inputs Supply Enterprise, Agricultural Equipment and Technical Services Share Company, Agricultural Mechanization Service Enterprise, and Natural Gum Processing and Marketing Enterprises.
Currently, the Corporation, which has several branch offices and six improved seed multiplication farms for various crops in different regions, is accountable to Ethiopian Investment Holdings and is also governed by a board of directors that supervises and controls the operations and business of the EABC as well.At present, EABC is playing its part in the implementation of the 10- year master plan for the agricultural sector at a national level. Based on this, it carries out agricultural activities ranging from land preparation to warehouse by providing integrated services through a single window, including agricultural inputs and mechanization services. In this regard, the Corporation supplies:
- Improved Seeds
- Solid and Foliar Fertilizers
- Agrochemicals and
- Veterinary Drugs to customers at affordable prices.
And also, the Corporation is striving to achieve its mission by rendering the following services:
- Agricultural Machineries with Original Spare Parts and Implements
- Construction Equipment
- Chemical and Fertilizer Spraying Machines
- Land development
- Agricultural Mechanization
- Seed Cleaning
- Repair Services for Agricultural and Construction Equipment
- Rental Services for Agricultural Machinery and Transport Vehicles (heavy goods transportation)
- Maintenance, Consulting, Technical/Vocational Training at the head office and its branches, along with after-sales services.
Additionally, Assembling Agricultural Equipment is also listed among the Corporation’s duties and responsibilities.
Furthermore, EABC is mandated to harvest, purchase, add value to, and process natural gum (GUM Arabic), as well as produce other forest products such as Gum Olibanum, Gum Myrrh & Gum Opoponax, supplying them to both domestic and international markets.
Since its establishment, the Corporation has achieved remarkable success in the agricultural sector. Building on these promising results, EABC has continued to play a vital role in modernizing agriculture, boosting production and productivity.
As a testament to its progress, the Corporation successfully met its authorized capital within a five-year period and a significant milestone that highlights its achievements in recent years. Its capital has now reached 7.564 billion birr.
Overall, the Corporation is making significant contributions to modernizing agricultural practices and enhancing productivity through integrated agricultural development activities, from land preparation to warehouse. And also by implementing the ISO 9001:2015 quality management system, the Corporation has achieved significant and encouraging results.
Purposes of establishment
The purposes for which the Corporation is established are:
- to buy from domestic and international markets and supply agricultural inputs; undertake agricultural inputs market price stabilization activities;
- to render agricultural mechanization services, agricultural and construction equipment repair services and provide rental services of agricultural machineries and transport vehicles;
- to buy from domestic and international markets and supply agricultural machineries and spare parts, construction equipment and agro-chemicals;
- to provide necessary education for the promotion of the use of modern agricultural machineries; provide consultancy service in handling and use of agricultural machineries and provide on the job technical trainings;
- to harvest, buy, value add to and process natural gum, produce other forest products, and supply to domestic and international markets;
- to undertake agricultural land development studies and preparation of designs, agricultural land surveying, clearing, leveling, drainage and irrigation activities as well as other activities related to agricultural land development;
- to cause undertaking of feasibility studies, design preparation, technology selection and negotiation, erection and commissioning of new and expansion projects as well as for research activities;
- to cause the local designing and manufacturing of agricultural machineries and spare parts in partnership with capable local and foreign companies;
- to work in cooperation with the concerned educational research and training institutions in producing trained manpower in such fields, numbers and quality as required by the sector;
- to undertake studies, based on direction given to it by the Ethiopian Investment Holdings, for the acquisition of financial, technological and modern governance inputs (including attracting investments or participating in investments) that can help it to become competitive, both locally and globally, and profitable and implement same upon approval;
- to multiply, clean and process pre-basic, basic and certified seeds of various crops, vegetables and fruits; where necessary import pre-basic seeds and cause their production or sale them; to sell byproducts;
- to undertake research and implement improvements with respect to the supply of agricultural inputs, agricultural machineries repair, the production and marketing of natural gum, mechanization services and related matters and thereby ensure its competitiveness;
- to sell bonds, collateralize, negotiate and sign loan agreements with local and foreign sources in accordance with directives issued by the Ministry of Finance and on the basis of the guidance of Ethiopian Investment Holdings;
- to engage in other related activities for the attainment of its purposes.
EABC’s mission, vision & values
Mission
Provide agricultural inputs and technologies that can significantly improve production and productivity, enhance modern farms and agro-industries at very competitive price to accelerate the nation’s economic development.
Vision
By providing integrated agricultural inputs and mechanization service, to become a strong competitor in Africa by 2030.
Values
- Loyalty
- Transparency
- Sincerity
- Commitment
- Mutual benefit
- Social responsibility
The products and services of EABC
Products
Improved seeds: EABC multiplies and supplies 22 crop species and 90 varieties to farmers, semi-pastoralists, investors and institutions.
Forest products: The Corporation offers forest products, including natural gum (GUM Arabic), Gum Olibanum, Gum Myrrh & Gum Opoponax for both local and international markets.
Fertilizers: EABC imports and distributes solid and liquid (including foliar) fertilizers to customers.
Agrochemicals and Chemical spraying equipment: The Corporation supplies herbicides, pesticides, fungicides, disinfectants and chemical spraying equipment.
Agricultural equipment, construction machinery and spare parts: The Company provides reliable and modern agricultural machinery and spare parts such as tractors, combine harvesters, furrowers, disc plows, tyres, inner tubes, batteries, filters, copper wires etc. It also offers construction machinery.
Services
- Integrated Agricultural Mechanization
- Land Development
- Seed Cleaning
- Maintenance Services for Farm Equipment, Trucks, Vehicles, and more
- Sales and Rental Services for Farm Equipment and Construction Machinery
- Heavy Goods Transport Rental Services
- Consultancy, Technical Training and Maintenance services to its customers along with after-sales services.
Human resource
The corporation currently employs a total of 1,635 staff members, comprising 1,363 permanent employees and 272 are contract workers.
Organizational Structure
EABC is mainly organized into four sectors:
- Agricultural Input Product and Supply Main Sector
- Agricultural Machineries and Products Supply Main Sector
- Resource Management Sector
- Chief Financial Office
These sectors are accountable to the Chief Executive Officer of the Corporation. Additionally, the structure includes five business units at the head office as well as several branch offices and stations located in various regions of the country, all operating under the main sectors. There are also 14 support units with distinct functions within the organization.

ማስታወቂያ
ለኢትዮጵያ የግብርና ልማት ተስማሚ የሆኑ የእርሻ መሣሪያዎች እና የግብርና ግብዓቶች – ከኢግሥኮ
ሁሌም ሙሉ፣ ዘወትርም ዝግጁ ሆኖ ወደሚጠብቅዎ የአርሶና አርብቶ አደሩ አለኝታ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ጎራ ይበሉና ለእርስዎ የንግድና የልማት ሥራዎች ይስማማሉ ብለን ያቀረብናቸውን ትራክተሮች፣ ኮምባይን ሀርቨስተሮች፣ ማረሻዎች፣ መከስከሻዎች፣ መስመር ማውጫዎች፣ ኬሚካል መርጫ ማሽኖች፣ የእርሻና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች መለዋወጫዎች፣ ጎማዎች፣ ባትሪዎች፣ ፊልትሮዎች፣ አግሮኬሚካሎች፣ ፈሳሽ ማዳበሪያዎች ወዘተ በተመጣጣኝ ዋጋ ገዝተው ያትርፉ።
ሁሌም በእናንተ ውድ ደንበኞቻችን ጥያቄና ፍላጎት ከታወቁ የውጭ ኩባንያዎች በምናስመጣቸው የእርሻና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች፣ አግሮኬሚካሎች፣ የእንስሳት መድኃኒቶች፣ ፈሳሽ ማዳበሪያዎችና መለዋወጫዎች፤ በምናቀርበው ምርጥ ዘር እንዲሁም በምንሰጠው የአንድ መስኮት አገልግሎት ቀዳሚ ተመራጭ ተቋም አድርጋችሁ ስለመረጣችሁን የላቀ ደስታና ኩራት እንደሚሰማን በዚህ አጋጣሚ በአክብርዎት ለመግለጽ እንወዳለን።
ለበለጠ መረጃ:- 0911 157091፣ 0911 223675
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!




























የኮርፖሬሽኑን ልማት ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ

አሶሳ፣ መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እያካሄደ የሚገኘውን የልማት ሥራ ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን የክልሉ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን አስታወቁ።ርዕሰ መስተዳድሩ ይህንን ያስታወቁት፣ በኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም የተመራ የልዑካን ቡድን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በአነጋገሩበት ወቅት ነው። ውይይቱ በዋነኛነት ያተኮረው ኮርፖሬሽኑ ለክልሉ ባቀረበው የበቆሎ ምርጥ ዘር ማባዣ የእርሻ መሬት ጥያቄ እና በተፈጥሮ ሙጫና እጣን ምርቶች አቅርቦት ላይ ነው።

በዚህ ወቅት አቶ አሻድሊ፣ ኮርፖሬሽኑ በ2013 ዓ.ም ለክልሉ አቅርቦ ለነበረው የምርጥ ዘር ማባዣ የእርሻ መሬት ጥያቄ ምላሽ በመስጠት መሬት መፍቀዳቸውን አስታውሰው፣ ይሁንና ኮርፖሬሽኑ የተፈቀደው መሬት ለበቆሎ ምርጥ ዘር እንደማይስማማ በመግለጽ ተለዋጭ መሬት መጠየቁን ተናግረዋል።
በዚህ መሰረት ቀደም ሲል ለኮርፖሬሽኑ ከተፈቀደው የእርሻ መሬት በተጨማሪ የኮርፖሬሽኑ እና የክልሉ የመሬት አስተዳደር ቢሮ ባለሞያዎች በጋራ ሆነው ጥናት በማካሄድ በአሶሳና ባምባሲ ዙሪያ ለበቆሎ ምርጥ ዘር ማባዣ ተስማሚ የሆነ የእርሻ መሬት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚያፈላልጉ ገልጸዋል።
የተፈጥሮ ሙጫና እጣን ምርቶችን ለኮርፖሬሽኑ ከማቅረብ አኳያም፣ በማኅበር ከተደራጁ የክልሉ ወጣቶች ጋር በመነጋገር ምርቶቹን እንዲያቀርቡ እንደሚደረግ አስታውቀዋል። በሌላ በኩል የክልሉን ግብርና በመደገፍ ረገድ ኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎችን ለክልሉ አርሶና አርብቶ አደሮች እንዲሁም ባለሃብቶች በማቅረብ፣ ሀገራዊ ተልዕኮውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
አክለውም ኮርፖሬሽኑ ከባለሃብቶች ጋር በመተባበር በኮንትራት እርሻ በክልሉ እያካሄደ ከሚገኘው የበቆሎ ምርጥ ዘር ብዜት በተጨማሪ የቅባት እህሎችን እንዲያመርት፣ የግብርና ግብዓቶችና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል እንዲያቋቁም፣ የዘር ብጠራ አገልግሎት እንዲሰጥ፣ የእርሻ መሣሪያዎች መለዋወጫዎች እንዲያቀርብ እና ከሽያጭ በኋላ የቴክኒክ ሞያ ሥልጠና እንዲያመቻች ጥሪ አቅርበዋል።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም በበኩላቸው፣ በቀጣይ የክልሉን የግብርና ልማት ይበልጥ ከማገዝ አኳያ የግብርና ግብዓቶችንና የእርሻ መሣሪያዎችን ከእነተቀጽላቸውና መለዋወጫቸው ጋር ለማቅረብ፣ ሁለገብ የግብርና ማዕከል ለማቋቋም፣ ለዜጓች ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ የዘር ብጠራ አገልግሎት እና የቴክኒክ ሞያ ሥልጠና ለመስጠት ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።በተለይም የክልሉ ባለሃብቶች፣ አርሶና አርብቶ አደሮች ኮርፖሬሽኑ ለገበያ የሚያቀርባቸውን የእርሻ መሣሪያዎች በብድር ገዝተው እንዲጠቀሙ ለማገዝ ከክልሉ ጋር በመሆን የባንክ ብድር የማመቻቸት ሥራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም የክልሉ መንግሥት ለኮርፖሬሽኑ ልማት ውጤታማነት እያደረገ የሚገኘውን ሁለገብ ድጋፍ አድንቀው፣ ምስጋና አቅርበዋል።በውይይቱ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበክር ኸሊፋ እና የርዕሰ መስተዳድሩ የኢኮኖሚ አማካሪ አቶ በቀለ አንበሳ እንዲሁም በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በኩል ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ክፍሌ ወልደማርያም፣ የእርሻ መሣሪያዎችና የግብርና ውጤቶች አቅርቦት ዐቢይ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፈለቀ ገዛኸኝ፣ የደን ውጤቶች አቅርቦትና ሽያጭ መምሪያ ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ብዙነሽ ኢያሱ እና የአሶሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ታደሰ ድሪርሳ ተገኝተዋል።
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!





ማስታወቂያ
ክቡራን ደንበኞቻችን፣
የአርሶና አርብቶ አደሩ አለኝታ የሆነው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት አዲስ አበባ በሚገኘው ዋና መ/ቤት ከሰኞ እስከ አርብ ከሚሰጠው መደበኛ አገልግሎት በተጨማሪ ከነገ ቅዳሜ መጋቢት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወር ሁለት ቅዳሜ ቀናትን ቢሮዎቹን ክፍት በማድረግ ሊያገለግላችሁ መዘጋጀቱን ሲገልጽ በታላቅ ደስታ ነው።
በዚህ መሰረት:- መጋቢት 6፣ መጋቢት 20፣ ሚያዝያ 4፣ ሚያዝያ 18፣ ግንቦት 2፣ ግንቦት 16፣ ሰኔ 7 እና ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጠዋት ከ2:00 – 6:00፤ ከሰዓት በኋላ ከ7:00 – 11:00 ድረስ ቢሮዎቻችን ክፍት ሆነው ይጠብቋችኋል።
ማስታወሻ
በቅርንጫፎቻችን ዘወትር ቅዳሜ ለደንበኞች የምንሰጠው አገልግሎት እንደተለመደው ይቀጥላል።
ይምጡ! በአገልግሎታችን ተደስተው ይመለሳሉ።
የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን

ለክቡራን ደንበኞቻችን የቀረቡ የአውሮፓ ስሪት የኬሚካል መርጫ መሣሪያዎች
ከአውሮፓ በአስመጣቸው ‘ዱዝ-ፋር’ እና ‘ዜቶር’ ትራክተሮች በደንበኞቹ ዘንድ ምስጋና እና አድናቆት የተቸረው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ)፣ እነሆ የገበያውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ በትራክተር የሚጎተቱ 3 ሺህ ሊትር አግሮኬሚካል የመያዝ አቅም ያላቸውን ጣልያን ሰራሽ ማሽኖች በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረቡን ሲገልጽ፣ ጥራት ላይ በመተማመን ነው። የጣልያኑ ሶጅማ ኩባንያ ምርት የሆኑት እነዚህ የኬሚካል መርጫ መሣሪያዎች 24 ሜትር ስፋት ያላቸው ሲሆን፣ ቁመታቸው እስከ 2 ሜትር ድረስ ከፍ ይላል። እርስዎ ቀድመው ይምጡና ይውሰዱ፤ እኛ ደግሞ ማገልገሉን እናውቅበታለን።
አድራሻ:- ወደ ቃሊቲ በሚወስደው ዋና መንገድ ከኢኳቴሪያል ቢዝነስ ግሩፕ ወይም ከፋፋ ምግብ አክስዮን ማኅበር 200 ሜትር ገባ ብሎ
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0114 – 423 438 ወይም 0911 157 091 ላይ ይደውሉ።






ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው! የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን

የቼክ ሪፐብሊክ ‘ዜቶር (ZETOR)’ ትራክተሮች ዛሬም በገበያ ላይ ናቸው

ከጣልያኑ ዱዝ-ፋር ትራክተር በተጨማሪ 110፣ 120 እና 136 የፈረስ ጉልበት ያላቸውን ‘ዜቶር’ በመባል የሚታወቁ የቼክ ሪፐብሊክ ታዋቂ ትራክተሮችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች አቅርቧል።ይሄም ብቻ አይደለም፤ ወደ ተቋማችን ጎራ ሲሉ ሌሎች ትርፋማ የሚያደርግዎትን ማረሻ፣ መከስከሻ፣ መስመር ዋውጫ፣ ኬሚካል መርጫ፣ ዘር መዝሪያ፣ ማዳበሪያ መበተኛ፣ የእርሻ መሣሪያዎችና የከባድ ተሽከርካሪዎች ጎማ፣ ባትሪ እና ፊልትሮ በተመጣጣኝ ዋጋ፣ በጥራትና በብዛት ያገኛሉ።
ለበለጠ መረጃ :- 0911 157091 ወይም 0114 – 42 34 38 ላይ ይደውሉ።










ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!
የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን