አለታ ወንዶ፣ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺእመቤት ነጋሽን ጨምሮ የተቋሙ አመራሮች ከሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሠራተኞች ጋር በመሆን በሲዳማ ክልል አለታ ወንዶ ወረዳ ሩንጃ ዊቾ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
“በጋራ ተስፋን እንትከል!” በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ላይ የደቡባዊ ሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ የሲዳማ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ፣ የአለታ ወንዶ ወረዳ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
###
በጋራ ተስፋን እንትከል!



