የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
  • Home
  • About Us
    • ስለ እኛ
    • About EABC
    • Board of Directors
    • Executive Management
    • Our Mission and Vision
    • Branch Offices
    • Headquarters Location
    • Organizational Structure
  • Products and Services
    • Agricultural Inputs
    • Seeds Products Supply
    • Forest Products Supply
    • Agriculture Equipment and Spare Part Supply
    • Agricultural Mechanization
    • Machinery & Heavy Duty Vehicles
  • Opportunities
    • Bids
  • Media & Publications
    • News
    • Accolades
    • Publications
    • Videos
  • Contact Us

የአርዳይታ የምርጥ ዘር እርሻ በዘር ተሸፈነ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአርዳይታ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻ ልማት 3081 ሄክታር መሬት በዘር ተሸፈነ።

የአርዳይታ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ አዲስ ጋረዶ እንደገለጹት፣ ለ2018/2019 የምርት ዘመን መሬቱን በዘር የመሸፈን ሥራ ሰኔ 9 ቀን ተጀምሮ ሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ተጠናቋል።

አሁን ላይ በአርዳይታ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻ ልማት 2 ሺህ 541 ሄክታር በስንዴ፣ 525 ሄክታር በጎመን ዘር እና 15 ሄክታር በገብስ የተሸፈነ ሲሆን፣ የዘር ሽፋን ሥራው በሦስት የዘር ደረጃዎችና በ17 ዝርያዎች ተከናውኗል።

በኮርፖሬሽኑ የሚተዳደረው የአርዳይታ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻ ልማት በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን ገደብ አሳሳ ወረዳ ይገኛል።
###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!

Twitter Facebook LinkedIn
Follow Us on Facebook

© 2026 Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

Powered by the ICT department of EABC