የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
  • Home
  • About Us
    • ስለ እኛ
    • About EABC
    • Board of Directors
    • Executive Management
    • Our Mission and Vision
    • Branch Offices
    • Headquarters Location
    • Organizational Structure
  • Products and Services
    • Agricultural Inputs
    • Seeds Products Supply
    • Forest Products Supply
    • Agriculture Equipment and Spare Part Supply
    • Agricultural Mechanization
    • Machinery & Heavy Duty Vehicles
  • Opportunities
    • Bids
  • Media & Publications
    • News
    • Accolades
    • Publications
    • Videos
  • Contact Us

የኮርፖሬሽኑ የ10 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ተገመገመ

ሀዋሳ፣ ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2018 በጀት ዓመት የ10 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ተገመገመ።

የኮርፖሬሽኑ ሥራ አመራር፣ የቅርንጫፍና ጣቢያ ሥራ አስኪያጆች እንዲሁም የሠራተኛ ማኅበር ሊቀመንበር በተገኙበት የተገመገመው አፈጻጸም ከገቢና ትርፍ አኳያ ከዕቅድ በላይ መሆኑ ተገልጿል።

ለውጤቱ መገኘት ባለፉት ጊዜያት የተከናወኑ የለውጥ ሥራዎች ተጠቃሽ መሆናቸውን የቀረበው የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያመለክታል።

የግምገማ መድረኩን የመሩት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ  ወይዘሮ የሺእመቤት ነጋሽ ለውጤቱ መገኘት የኮርፖሬሽኑን የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች አመስግነው፣ በዕቅድ የተያዙ ቀሪ ሥራዎችን በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ለማሳካት ርብርብ እንዲደረግ አሳስበዋል።

አክለውም የኮርፖሬሽኑን ዓላማና ግብ ለማሳካት የተጀመሩ የለውጥ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መልእክት አስተላልፈዋል።
               ###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!

Twitter Facebook LinkedIn
Follow Us on Facebook

© 2026 Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

Powered by the ICT department of EABC