የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
  • Home
  • About Us
    • ስለ እኛ
    • About EABC
    • Board of Directors
    • Executive Management
    • Our Mission and Vision
    • Branch Offices
    • Headquarters Location
    • Organizational Structure
  • Products and Services
    • Agricultural Inputs
    • Seeds Products Supply
    • Forest Products Supply
    • Agriculture Equipment and Spare Part Supply
    • Agricultural Mechanization
    • Machinery & Heavy Duty Vehicles
  • Opportunities
    • Bids
  • Media & Publications
    • News
    • Accolades
    • Publications
    • Videos
  • Contact Us

ኮርፖሬሽኑ ለቀን ሠራተኞች ማእድ አጋራ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በዋና መ/ቤትና በአዳማ ቅርንጫፍ ለሚያገለግሉ 126 የቀን ሠራተኞች ማእድ አጋራ።

በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ለተካሄደው ማእድ ማጋራት ከ600 ሺህ ብር በላይ ወጪ የምግብ ዘይትና አልባሳት የተገዛ ሲሆን፣ አይሚ ገዳ የምግብ ኮምፕሌክስ የተባለ ድርጅት በስፖንሰርነት 20 ኩንታል የስንዴ ዱቄት ድጋፍ አድርጓል።

ኮርፖሬሽኑ ወደ ውጭ ገበያ በሚልከው የእጣንና የሙጫ ምርት ዝግጅት ላይ ለተሰማሩ 37 የአዳማ ቅርንጫፍ ሴት የቀን ሠራተኞች ከማእድ ማጋራት በተጨማሪ አልባሳት ተበርክቶላቸዋል።

በዕለቱ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ የሺእመቤት ነጋሽ ባስተላለፉት መልእክት፣ በሀገረ መንግሥት ግንባታና በሰላም ማስፈን ረገድ የሴቶች ተሳትፎና ጥበብ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው፣ በቀጣይም ሴቶች ከወንድ አጋሮቻቸው ጋር በመሆን የሀገሪቷን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያበረክቱ አሳስበዋል።

በተለይም ግብርናን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ ውስጥ የኮርፖሬሽኑ ሴቶች ግንባር ቀደም ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አስተላልፈዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የአዳማ ቅርንጫፍ ሴት የቀን ሠራተኞች በሰጡት አስተያየት “ተረስተን ነበር፤ አሁን ግን አስታዋሽ በማግኘታችን እናመሰግናለን” ብለዋል።

በኮርፖሬሽኑ የሥርዓተ ጾታ እኩልነትን እና የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት በሞያ ደኅንነትና ጤንነት አገልግሎት ቡድን መሪ ወ/ሮ ወይንሸት ገለሶ የቀረበ ሲሆን፣ በሥርዓተ ጾታና ሴቶችን በማብቃት ዙሪያ በሒሩት በቀለ (ዶ/ር) ገለጻ ተደርጓል።
###
50 ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለፀገች ኢትዮጵያ!

Twitter Facebook LinkedIn
Follow Us on Facebook

© 2025 Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

Designed and Developed by the ICT department of EABC