አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13/2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን 850 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ዋጋ ያላቸውን የእርሻ መሣሪያዎች ለኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት (ኤ ቲ አይ) በሽያጭ አቀረበ።

የግብርና ሚኒስቴር ለክልሎች በድጋፍ መልክ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ካስረከባቸው የግብርና ሜካናይዜሽን ማሽነሪዎች ውስጥ ኮርፖሬሽኑ ለኤ ቲ አይ ያቀረባቸው የእርሻ መሣሪያዎች በዋናነት ይጠቀሳሉ።

ኮርፖሬሽኑ ካቀረባቸው የእርሻ መሣሪያዎች ውስጥ 41 ዜቶር እና ዲዩዝ ፋር ተብለው የሚታወቁ የአውሮፓ ስሪት ትራክተሮች የሚገኙ ሲሆን፣ የፈረስ ጉልበታቸው 117፣ 120፣125 እና 143 ነው።
የግብርና ሚኒስቴር የእርሻ መሣሪያዎችን፣ ተሸከርካሪዎችንና ኮምፒውተሮችን ለክልሎች በድጋፍ መልክ ባስረከበበት ወቅት የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺእመቤት ነጋሽ ተገኝተዋል።
###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!
