ጅማ፣ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በሚያቀርባቸው የግብርና ግብዓቶችና በሚሰጠው የሜካናይዜሽን አገልግሎት ዙሪያ በኦሮሚያና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሎች ከሚገኙ የባለድርሻ አካላት ጋር የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በጅማ ከተማ ውይይት ተደረገ።
የውይይቱ ተሳታፊዎች ከኦሮሚያ ክልል ከምዕራብ ሸዋ፣ ከምስራቅ ወለጋ፣ ከሆሮ ጉድሩ ወለጋ፣ ከቄለም ወለጋ፣ ከምዕራብ ወለጋ፣ ከቡኖ በደሌ፣ ከኢሉ አባቦርና ጅማ ዞኖች እንዲሁም ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከስድስት ዞኖች የተውጣጡ ናቸው።
###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!












