አዲስ አበባ፣ የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ):-የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን እና የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በምግብ እህል ምርትና አቅርቦት በጋራ ለመሥራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ተወያዩ።
በውይይቱ ወቅት ኮርፖሬሽኑ ኮሚሽኑ በመጠባበቂያ የሚያከማቸውንና ለዕለት ደራሽ እርዳታ የሚያሰራጨውን የምግብ እህል (ስንዴ፣ በቆሎና ሩዝ) አምርቶ እንዲያቀርብ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያለው 54 ሺህ ኩንታል ስንዴ በሽያጭ ለኮሚሽኑ ቀርቧል፡፡
በውይይቱ ላይ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺእመቤት ነጋሽ፣ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) እና የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!



