የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
  • Home
  • About Us
    • ስለ እኛ
    • About EABC
    • Board of Directors
    • Executive Management
    • Our Mission and Vision
    • Branch Offices
    • Headquarters Location
    • Organizational Structure
  • Products and Services
    • Agricultural Inputs
    • Seeds Products Supply
    • Forest Products Supply
    • Agriculture Equipment and Spare Part Supply
    • Agricultural Mechanization
    • Machinery & Heavy Duty Vehicles
  • Opportunities
    • Bids
  • Media & Publications
    • News
    • Accolades
    • Publications
    • Videos
  • Contact Us

የኮርፖሬሽኑ የነባራዊ ሁኔታ የዳሰሳ ጥናት ሪፖርት ለውይይት ቀረበ

ቢሾፍቱ፣ ታህሳስ 25/2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በሦስት የዳሰሳ ጥናት ቡድኖች ሲያካሂድ የቆየው የተቋሙ የነባራዊ ሁኔታ የዳሰሳ ጥናት ለኮርፖሬሽኑ ሥራ አመራር ለውይይት ቀረበ።

ውይይቱ ከዛሬ ታህሳስ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ቢሾፍቱ በሚገኘው ያዴን ሆቴል ይቀጥላል።

በጥቅምት ወር መጨረሻ የተጀመረው የዳሰሳ ጥናት ዋና ዓላማ፣ የኮርፖሬሽኑን አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታ በመገምገም ተቋሙ በቀጣይ በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ፣ ምርታማና አትራፊ ሆኖ እንዲቀጥል ለማስቻል መሆኑን የጥናት ሪፖርቱን ያቀረቡት የኮርፖሬሽኑ የእርሻ መሣሪያዎችና የግብርና ውጤቶች አቅርቦት ዐቢይ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተከስተ ክፍሌ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

የዳሰሳ ጥናቱ ድርጅታዊ መዋቅር እንዲሁም የሰው ኃይል አስተዳደር፤ የአሠራር ሥርዓትና ሂደቶች፤ የአቅርቦትና ንብረት አስተዳደር፤ የማዳበሪያ፣ የአግሮኬሚካሎች፣ የምርጥ ዘር፣ የግብርና ውጤቶች፣ የተፈጥሮ ሙጫ ምርቶችና የእርሻ መሣሪያዎች አቅርቦት፤ የሜካናይዜሽን፣ የትራንስፖርትና የጥገና አገልግሎቶች፤ ገበያና ሽያጭ፤ የፋይናንስ አሠራርና የመረጃ አስተዳደር ሥርዓት መስኮችን ያካተተ መሆኑን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።

በጥናቱ ችግሮች፣ ጥንካሬዎች፣ መልካም አጋጣሚዎችና ስጋቶች መለየታቸውን ያስታወቁት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ የተቋሙን መዋቅራዊ አደረጃጀት በመፈተሽ፤ የዋና መ/ቤት፣ የዘርፎችና የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የሥራ መሪዎችና ከፍተኛ ባለሞያዎችን በመጠየቅ እንዲሁም ውስጣዊና ውጫዊ መረጃዎችን በመተንተን ጥናቱ መከናወኑን አብራርተዋል።

በመጨረሻም በጥናት ግኝት የተለዩ ቁልፍ ችግሮችን፣ የችግሮቹ መነሻ መንስኤዎችን፣ ያሳደሩት ተጽዕኖዎችን፣ የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎችን እንዲሁም ጠንካራ ጎኖችን፣ ክፍተቶችን፣ መልካም እድሎችን እና ስጋቶችን መሰረት በማድረግ ምክረ ሀሳቦች መቅረባቸውን አስታውቀዋል።

በውይይቱ ላይ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺእመቤት ነጋሽን ጨምሮ የተቋሙ ሥራ አመራር እና የጥናት ቡድን አባላት ተገኝተዋል።

                     ###

     ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!

Twitter Facebook LinkedIn
Follow Us on Facebook

© 2025 Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

Designed and Developed by the ICT department of EABC