የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
  • Home
  • About Us
    • ስለ እኛ
    • About EABC
    • Board of Directors
    • Executive Management
    • Our Mission and Vision
    • Branch Offices
    • Headquarters Location
    • Organizational Structure
  • Products and Services
    • Agricultural Inputs
    • Seeds Products Supply
    • Forest Products Supply
    • Agriculture Equipment and Spare Part Supply
    • Agricultural Mechanization
    • Machinery & Heavy Duty Vehicles
  • Opportunities
    • Bids
  • Media & Publications
    • News
    • Accolades
    • Publications
    • Videos
  • Contact Us

መልካም ሥነ ምግባር የተላበሱ አመራሮችና ሠራተኞች ለተቋም ስኬት መሠረት ናቸው።

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- መልካም ሥነ ምግባር የተላበሱ አመራሮችና ሠራተኞች ለተቋም ስኬት መሠረት መሆናቸውን የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ።

ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ወ/ሮ የሺእመቤት ነጋሽ ይህንን የገለጹት፣ ለኮርፖሬሽኑ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች  ከታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት በዋናው መ/ቤት በተዘጋጀ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና የሥልጠና መርሐ ግብር ላይ ነው።

ወ/ሮ የሺእመቤት ሥልጠናውን ሲከፍቱ ባስተላለፉት መልእክት፣ የኮርፖሬሽኑ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች መልካም ሥነ ምግባርን በመላበስ፣ ሙስናን በመጸየፍና ብልሹ አሠራርን በመከላከል ኃላፊነትን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

አክለውም ኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ የሀገር ሀብትና ንብረት የሚያንቀሳቅስና ለሀገሪቷ ኢኮኖሚያዊ እድገት የጀርባ አጥንት የሆነ ስትራቴጂካዊ ተቋም በመሆኑ ሕጎችን፣ መመሪያዎችንና ተገቢ አሠራሮችን ጠብቆ ሥራዎችን ማከናወን እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ከፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ይህ ሥልጠና፣ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የኮሚሽኑ ተባባሪ አሠልጣኝ ዘመዴ ዛኪ (ዶ/ር) አማካኝነት እየተሰጠ ነው፡፡
                    ###
   ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!

Twitter Facebook LinkedIn
Follow Us on Facebook

© 2025 Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

Designed and Developed by the ICT department of EABC