ቦንጋ፣ ታህሳስ 4 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) የተመራ የልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በቦንጋ ከተማ ያስገነባውን የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ጎበኘ።
የልዑካን ቡድኑ በማዕከሉ የሚካሄደውን የምርጥ ዘር ዝግጅት ተመልክቷል።
በጉብኝቱ ላይ አቶ ሳዳት ነሻ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ፣ አቶ ፍቅሬ አማን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ እንዲሁም የካፋ ዞንና የቦንጋ ከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!








