አዲስ አበባ፣ ህዳር 22 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፈበት 12ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የኢትዮጵያ የጥራት ሽልማት ውድድር ላይ የአድናቆት የምስክር ወረቀት/Honorary Certificate/ አግኝቷል።
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት ህዳር 20 ቀን 2018 ዓ.ም በብሔራዊ ቤተ መንግሥት በተካሄደው የሽልማት ሥነ ሥርዓት ላይ አቶ አወቀ ደጉ ኮርፖሬሽኑን በመወከል ሽልማቱን ተቀብለዋል።
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!
