አዲስ አበባ፣ መስከረም 20/2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከተቋሙ የሥራ አመራር ጋር ትውውቅ አደረጉ።
ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ወይዘሮ የሺእመቤት ነጋሽ መስከረም 20/2018 ዓ.ም በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ተገኝተው ከሥራ አመራሩ ጋር ተዋውቀዋል።
በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፣ ኮርፖሬሽኑ ግብርናን በማዘመንና የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደተጣለበት አስታውቀው፣ በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩና አዳዲስ የልማት ሥራዎችን በጋራ ጥረት ይበልጥ ውጤታማ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ይህንን ለመፈጸም ኮርፖሬሽኑ በሰው ኃይል፣ በአደረጃጀት፣ በአሠራርና በሀብት የተሟላ እንደሆነ መረዳታቸውን ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ነገ ረቡዕ መስከረም 21/2018 ዓ.ም የኮርፖሬሽኑን ሠራተኞች እንደሚያነጋግሩ ይጠበቃል።
በተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊነት ቦታዎች ሀገራቸውን ያገለገሉት ወይዘሮ የሺእመቤት ነጋሽ ከመስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተመድበዋል።
###
ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!






