አዲስ አበባ፣ መስከረም 15/2018 ዓ.ም (ኢግሥኮ):- የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ለኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን መስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም በጻፈው ደብዳቤ እንዳሳወቀው፣ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ አመራር ቦርድ በአዲስ መልክ ተደራጅቷል።
በዚህ መሰረት ከመስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ:-
ክብርት ወ/ሮ ዓለምፀሀይ ጳውሎስ – የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር – የቦርድ ሰብሳቢ
ክቡር አቶ አዲሱ አረጋ – የኢፌዴሪ የግብርና ሚኒስትር – የቦርድ ምክትል ሰብሳቢ
ክብርት ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው – በኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ትብብር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ – የቦርድ አባል
ክቡር ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) – የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ – የቦርድ አባል
ክቡር አቶ አቤ ሳኖ – የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት – የቦርድ አባል
ክቡር ታከለ ኡማ (ኢ/ር) – የኢትዮ – ጂቡቲ የምድር ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ – የቦርድ አባል
ክቡር ማንደፍሮ ንጉሤ (ዶ/ር) – የኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር – የቦርድ አባል
አቶ ኪያ ተካልኝ – ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ – የቦርድ አባል
አቶ ዳንኤል ስለሺ – በኮርፖሬሽኑ ሠራተኞች የተመረጡ – የቦርድ አባል ሆነው ተመድበዋል።
ዝርዝሩን ለመመልከት እባክዎ ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ።
የኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት