የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
Ethiopian Agricultural Businesses Corporation
  • Home
  • About Us
    • ስለ እኛ
    • About EABC
    • Board of Directors
    • Executive Management
    • Our Mission and Vision
    • Branch Offices
    • Headquarters Location
    • Organizational Structure
  • Products and Services
    • Agricultural Inputs
    • Seeds Products Supply
    • Forest Products Supply
    • Agriculture Equipment and Spare Part Supply
    • Agricultural Mechanization
    • Machinery & Heavy Duty Vehicles
  • Opportunities
    • Bids
  • Media & Publications
    • Accolades
    • Publications
    • Videos
  • Contact Us

በ2016 እቅድ አፈጻጸም እና በ2017 እቅድ ዙሪያ ውይይት ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢግሥኮ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች በ2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና በ2017 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ነሐሴ 21 ቀን 2016 ዓ.ም በኮርፖሬሽኑ ዋና መስሪያ ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተወያዩ።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም የኮርፖሬሽኑ የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች ባደረጉት ሁለገብ ጥረት ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት ያቀዳቸውን ሥራዎች ማሳካት መቻሉን አስታውቀዋል፡፡ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለተገኘው ውጤት የሥራ መሪዎችን እና ሠራተኞችን አመስግነው፣ በተያዘው በጀት ዓመት በከፍተኛ ቁርጠኝነት በመስራት የኮርፖሬሽኑን ስኬታማ ጉዞ እንዲያስቀጥሉ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡አክለውም በተፈጥሮ ሙጫ ምርቶች አቅርቦት፣ በመሬት ዝግጅት፣ በሰብል መሰብሰብ፣ በተሽከርካሪዎች ጥገና ጥራት እና በፕሮጀክቶች አፈጻጸም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት መስራት ይጠበቃል ብለዋል፡፡የምርት እና አገልግሎት አይነትና መጠንን ማስፋት እና ወጪ ቅነሳ ሌሎች የበጀት ዓመቱ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውንም ዋና ሥራ አስፈጻሚው አስገንዝበዋል፡፡በዕለቱ ከሠራተኞች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ዋና ሥራ አስፈጻሚው እና ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
                              ###
              ግብርናን ማዘመን ግባችን ነው!

Twitter Facebook LinkedIn
Follow Us on Facebook

Copyright 2024 Ethiopian Agricultural Businesses Corporation

Designed and Developed by the ICT department of EABC