በኢንተርሌግዠሪ ሆቴል መጋቢት 24/2015 ዓ.ም. በተዘጋጀ የኢንደስትሪ ሽልማት መርሐ ግብር ላይ ኮርፖሬሽኑ የወርቅ ዋንጫ፣ የወርቅ ሜዳሊያ እና ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ አግኝቷል። ሽልማቱን ከዕለቱ የክብር እንግዳ የኢፌዴሪ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) እጅ የተቀበሉት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ናቸው።

በተመሳሳይ  የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም በግላቸው የሥራ አመራር ከፍተኛ የክብር ኮርደን/GOLD Honor CORD ሽልማት እና በኢንደስትሪ ሥራ አመራር የላቀ አፈጻጸም የክብር ዲፕሎማ (Diploma of the Legion of Honour) ከቀድሞ ፕሬዝዳንት እጅ ተቀብለዋል። እንዲሁም የኮርፖሬሽኑ የኦፕሬሽን ዐቢይ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፈለቀ ገዛኸኝ ከቀድሞ ፕሬዝዳንት እጅ  የወርቅ ኒሻንና የትጉህ አመራር የክብር ዲፕሎማ ተሸልመዋል። በተጨማሪም ሦስት አመራሮችና ዘጠኝ ሠራተኞች የወርቅ ሜዳሊያና የትጉህ ሠራተኝነት የክብር ዲፕሎማ ከአቢሲኒያ የጥራት ሽልማት ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አሰፋ ከሲቶ እጅ ተቀብለዋል።

በሽልማት መርሐ ግብሩ ላይ የዕለቱን የክብር እንግዳ የኢፌዴሪ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) ጨምሮ ሚኒስትሮች፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የኢንደስትሪ ተቋማት አመራሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ተሽላሚዎችና ቤተሰቦቻቸው ተገኝተዋል። በኮርፖሬሽኑ በኩል በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ የሥራ አመራር ቦርድ አባል አቶ ወልደአብ ደምሴ፣ በሠራተኛ የተመረጡ የቦርድ አባላት፣ የመሰረታዊ የሠራተኛ ማኅበር ሓላፊዎች፣ የማኔጅመንት አባላት እና ሠራተኞች ተገኝተዋል።

“ዓለምንና ሕዝቦቿን የሚታደግ የላቀ ሥራ ለሰሩ ትጉሃን እንሸልማለን!” የሚል መሪ ቃልን አንግቦ በተለያዩ የሞያ መስኮች መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦችን በየዓመቱ በመሸለም የሚታወቀው “አቢሲኒያ ዓለም አቀፍ ሽልማት ድርጅት” ከ2010 እስከ 2014 ዓ.ም. ድረስ ባደረገው ጥናት ለመጀመሪያ ጊዜ ለኢንደስትሪ ሽልማት ካጫቸው ከ57 ሺህ በላይ አምራች እና አገልግሎት ሰጪ የመንግሥት፣ የግል እና ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ውስጥ 50 ተሸላሚዎችን የመረጠ ሲሆን፣  የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) አንዱ በመሆን ተሸልሟል።

በአቢሲኒያ የጥራት ሽልማት ድርጅት የተሸለሙ የኢግሥኮ ትጉሃን የሥራ አመራሮችና ሠራተኞች ስም ዝርዝር

1.
 አቶ ክፍሌ ወልደማርያም
2. አቶ ፈለቀ ገዛኸኝ
3. አቶ ዘነበ ወልደሥላሴ
4. አቶ ሰለሞን ገብሬ
5. ወይዘሮ መንበረ ኃይለማርያም
6. ወይዘሮ አመለወርቅ ዓለምአየሁ – ከግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ
7. ወይዘሮ ነፃነት ረቡማ – ከግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ
8. አቶ ተስፋሁን አበበ አንጀሎ – ከእርሻ መሣሪያዎችና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ
9. አቶ ሲራክ ደገፋ – ከእርሻ መሣሪያዎችና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ
10. አቶ ሲዳ ለታ – ከኢትዮጵያ ምርጥ ዘር እና ደን ውጤቶች ዘርፍ
11. አቶ ሻምበል ገላን – ከኢትዮጵያ ምርጥ ዘር እና ደን ውጤቶች ዘርፍ
12. አቶ ግርማ ፋሪስ – ከተሽከርካሪዎች አስተዳደርና ጥገና ዘርፍ
13. አቶ ተከስተ ተክሌ – ከተሽከርካሪዎች አስተዳደርና ጥገና ዘርፍ
14. አቶ ዳንኤል ስንሻው – ከዋናው መ/ቤት

አቢሲኒያ የጥራት ሽልማት አሰጣጥ መርሐ ግብር